ሴናተር ሊዲያ ቶርፕ ከግሪንስ ፓርቲ የአውስትራሊያ ሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ምክትል መሪነታቸው ለቀቁ

የአውስትራሊያ ይፋ ሥራ አጥነት ቁጥር 3.5 ፐርሰንት ላይ ረግቷል።

Greens senator and DjabWurrung Gunnai Gunditjamara woman Lidia Thorpe.jpg

Greens senator and DjabWurrung Gunnai Gunditjamara woman Lidia Thorpe. Credit: SBS News / NITV

የግሪንስ ፓርቲ ሴናተር ከነበራቸው የፓርላማ ኃላፊነትና የፍቅር ግንኙነታቸው መስመሮች የሚጣረሱ በመሆኑና የፈፀሙት ተግባርም "ስህተት" መሆኑን አምነው በመቀበል ከፓርላማ ኃላፊነታቸው ለቅቀዋል።

ሆኖም፤ በግሪንስ ፓርቲ የነባር ዜጎች ጉዳይ ተጠሪነታቸው ይቀጥላሉ።

የሴናተር ቶርፕ ጽሕፈት ቤት ሠራተኞች ከአንድ በወንጀል ንኪኪ ተጠርጣሪ የሞተር ብስክሌት ቡድን የቀድሞ መሪ ጋር ያላቸው የፍቅር ግንኙነት ከፓርላማ የሕግ አስከባሪ ኮሚቴ አባልነታቸው ጋር እንደሚፃረር ቢነግሯቸውም ቸል ብለው የፍቅር ግንኙነታቸውን ቀጥለው ነበር።

ወ/ሮ ቶርፕ በአባልነት ያሉበት የፓርላማ ኮሚቴ የሞተር ብስክሌትና የተደራጁ የወንጀል ቡድኖችን አስመልክቶ ምስጢርነቱ ከፍ ያለ የመረጃ ማብራሪያን የሚያደምጥ ኮሚቴ ነው።

የሥራ አጥነት ቁጥር

የአውስትራሊያ ይፋ ሥራ አጥነት ቁጥር 3.5 ፐርሰንት ላይ ረግቷል።

 የአውስትራሊያ ስታቲስቲክስ ቢሮ ዛሬ ይፋ እንዳደረገው ባለፈው ወር 900 አዳዲስ ሥራዎች ተፈጥረዋል።

በሕመም ሳቢያም የሐኪም ፈቃድ በመውሰድ በሥራ ገበታቸው ላይ የማይገኙ ሠራተኞች ቁጥር ቀንሷል።

ይሁንና የሥራ ሚኒስትር ቶኒ በርክ፤ የሴፕቴምበር ወር የሥራ አጥነት ቁጥር የሚያሳየን በደመወዝ ዕድገትና በሥራ አጥነት ቁጥር ዝቅተኝነት መካከል ያሉት ግንኙነቶች አለመሰናሰላቸውን ነው ብለዋል።

የወቅቱ የአውስትራሊያ የደመወዝ አመላካች አሃዝ 2.6 ነው።

 




Share

Published

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service