የሌበር ፓርቲ መሪ አንቶኒ አልባኒዚ ዛሬ ማምሻውን በኮቪድ-19 መጠቃታቸውን አስታወቁ።
በጤና መምሪያ መሠረት ለመጪዎቹ ሰባት ቀናት ከአደባባይ የምርጫ ዘመቻ ራሳቸውን አግልለው ይቆያሉ።
አቶ አልባኒዚ በቫይረሱ መያዛቸው የተገለጠው ወደ ምዕራብ አውስትራሊያ ሔደው የምርጫ ዘመቻቸውን ለማካሔድ በመሰናዶ ላይ ሳሉ ነው።
የሌበር ፓርቲ መሪው ድንገት በኮቪድ-19 ቢያዙ አማራጭ የምርጫ ዘመቻ ፕላኖች ያሉት ሲሆን፤ በነገው ዕለት የትኛውን አማራጭ እንደሚጠቀም ይፋ ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል።
Share

