ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን የኦቲዝም ተጠቂ ልጅን አስመልክተው ለሰነዘሩት አተያይ ይቅርታ ጠየቁ

*** በመጀመሪያው ዙር የመሪዎች ክርክር የሌበር መሪ አሸነፉ

News

Source: AAP

ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን እሳቸውና ባለቤታቸው የግብረ አካል ጉዳተኛ ባልሆኑ ሁለት ልጆች "መባረካቸውን" አስመልክተው መናገራቸው ብርቱ ትችት አስዘንዝሮባቸዋል። 

አቶ ሞሪሰን ሁለት ልጆቻቸውን አንስተው መናገራቸው ጭብጣቸውን ለማስረዳት ሲሉ እንጂ በተቃራኒው አለመሆኑን ጠቅሰው ሰዎች በዚያ መልኩ እንዲረዷቸው አመላክተዋል። ይቅርታም ጠይቀዋል።  

ጠቅላይ ሚኒስትሩን ለትችትና ይቅርታ ያጋለጠው የአራት ዓመት ኦቲዝም ተጠቂ ልጅ እናት የሆኑት ካትሪን ዮማን ትናንት ምሽት ብሪስበን በተካሔደው የመጀመሪያው የመሪዎች ክርክር ወቅት ተገኝተው ላቀረቡት ጥያቄ መልስ በሰጡበት ወቅት ነው።

ወ/ሮ ዮማን ጥያቄያቸውን ለመንሳት ግድ የተሰኙት ልጃቸው 30 ፐርሰንት ወይም በሺህዎች የሚቆጠር የግብረ አካል ጉዳተኞች ድጎማ የተቀነሰበትና ገና ለየትኛው ፓርቲ ድምፃቸውን እንደሚሰጡ ከውሳኔ ላይ የደረሱ ባለመሆኑ ጭምር ነው።    

የአቶ ሞሪሰን ምላሽ የዘንድሮው የዓመቱ አውስትራሊያዊና የግብረ አካል ጉዳተኛው ዲለን አልኮትንም "ለእኛና ለቤተሰቦቻችን ማዘን ምንም አይጠቅምም። የሚጠቅመው እኩል ክብካቤ ስናገኝና በሕይወታችን ላይ ቁጥጥር እንዲኖረን ምርጫ እንዲኖረን ማድረግ ሲቻል ነው" የሚል ምላሽ እንዲሰጥ ገፋፍቶታል። 

ጠቅላይ ሚኒስትሩም አልኮትን በግል ይቅርታ ጠይቀዋል። 

ወ/ሮ ዮማን አቶ ሞሪሰን ከመሪዎች የመጀመሪያው ክርክር በኋላ በግል እንዳነጋገሯቸው አንስተው ሆኖም ለጥያቄያቸው ቀጥተኛ ምላሽ እንዳልሰጧቸው ተናግረዋል። 

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ቃላቶች የሳቸውን ጥያቄ እንዲያደበዝዝ እንደማይሹም አሳስበዋል።

ትናንት ምሽት ላይ በሌበር መሪ አንቶኒ አልባኒዚና ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን መካከል በተካሔደው የመጀመሪያው የመሪዎች ክርክር አቶ አልባኒዚ 40፣ አቶ ሞሪሰን 35 ድምፆችን ከታዳሚዎች አግኝተዋል።

Anthony Albanese muss sich nach einem positiven PCR Test in Isolation begeben
Leader of the Opposition Anthony Albanese (L) and Australian Prime Minister Scott Morrison attend the first leaders' debate of the 2022 federal election. Source: Getty

ድምፁን የሰጡት የትኛውን ፓርቲ እንደሚመርጡ ገና ከውሳኔ ላይ ያልደረሱና በመሪዎቹ ክርክር ላይ ታድመው ጥያቄዎችን በማንሳት ከክርከሩ ፍፃሜ በኋላ ለየትኛው ፓርቲ ድምፃቸውን ለመስጠት እንደወሰኑ ከተጠየቁት 100 ሰዎች ውስጥ ነው።

ክርክሩን ከተከታተሉት ውስጥ 25ቱ አሁንም ከውሳኔ ላይ አልደረሱም።     

በክርከሩ ወቅት የግብረ አካል ጉዳተኞችን ጨምሮ የምጣኔ ሃብት፣ የፀረ ሙስና ኮሚሽን ምስረታ፣ የቻይናና የድንበር ጥበቃ ጉዳዮች ሰፋ ያለ ክርክር ተካሂዶባቸዋል።  

 

 

 

 


2 min read

Published

Updated

By NACA

Presented by Kassahun Seboqa Negewo


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now