በሞቃዲሾ ሆቴል በደረሰ ጥቃት የሟቾች ቁጥር 20 መድረሱና የአል-ሻባብ ታጣቂዎች መደምሰሳቸው ተገለጠ

አለባበሷ ወግ የጠበቀ አይደለም በሚል ለእሥር የተዳረገችው ሩዋንዳዊት በዋስ መለቀቋ ተነገረ

Security officers patrol near the the site of explosions in Mogadishu.jpg

Security officers patrol near the the site of explosions in Mogadishu on August 20, 2022. Credit: HASSAN ALI ELMI/AFP via Getty Images

የአልሻባብ ሚሊሺያ ቡድን አባላት በሞቃዲሾ ሃያት ሆቴል በሰነዘሩት ጥቃት ሳቢያ ሕይወታቸው ያለፈ ሰዎች ቁጥር ወደ 20 ከፍ ማለቱና 40 ሰዎች ላይ የመቁሰል አደጋ መድረሱ ተገለጠ።

ሆቴሉ በሶማሊያ ምክር ቤት አባላትና የመንግሥት ባለልጣናት የሚዘውተር ሲሆን፤ የሟቾቹና የቁስለኞች ማንነት እስካሁን ይፋ አልሆነም።

የተኩስ ጥቃቱ የጀመረው በሁለት መኪናዎች ውስጥ የተጠመዱ ፈንጂዎች ፍንዳታን ተከትሎ ነው።

የአልሻባብ ቡድን ከአልቃይዳ ጋር ትስስር ያለው ሲሆን ለጥቃቱም ኃላፊነቱን ወስዷል።

 የፀጥታ ኃይል ባለስልጣናት ለአንድ ምሽት ሆቴሉንና ሰላማዊ ስዎችን በቁጥጥራቸው ስር አድርገው የነበሩ ሚሊሺያዎችን ደምስሰው ሆቴሉንና አካባቢውን በቁጥጥራቸው ስር ማድረጋቸውን አስታውቀዋል።

በሌላ በኩል ግና የፀጥታ ኃይላቱ አካክባቢውን ሙሉ ለሙሉ በቁጥጥራችው ስር ለማድረግ እየጣሩ መሆኑ ይነገራል።

***

የ24 ዓመቷ ሩዋንዳዊት ሊሊያን ሙጋቤካዚ ኦገስት 7 በፈረንሳዊው ሙዚቀኛ ታይክ ኮንሰርት ላይ በተገኘችበት ወቅት አለባበሷ ወግ የጠበቀ አይደለም በሚል ዘብጥያ ወርዳለች።

ሊሊያን በአለባበሷ ሳቢያ ክስ ተመስርቶባት ፍርድ ቤት በቀረበችበት ወቅት የዋስ መብት የተነፈጋት ቢሆንም ትናንት የዋስ መብቷ ተጠብቆ መለቀቋ ተነግሯል።

በአለባበሷ ምክንያት ጥፋተኛ ሆና ከተገኘች ግና እስከ ሁለት ዓመት የሚደርስ የእሥር ብይን ሊጣልባት ይችላል።

Share

Published

Updated

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service