አውስትራሊያ ድንበሯን ከፍታ ዓለም አቀፍ መንገደኞችን መቀበል ጀመረች

***የእንግሊዟ ንግሥት ኤልሳቤጥ በኮቪድ-19 ተጠቁ

News

Charlotte Roempke welcomes her grand father Bernie Edmonds as he arrives at Sydney International Airport. Source: AAP

የአውስትራሊያ ዓለም አቀፍ ድንበር ከዛሬ ሰኞ ፌብሪዋሪ 21 ጀምሮ ክፍት ሆኗል። 

የኮቪድ-19 መከላከያ ክትባቶችን የተከተቡ የባሕር ማዶ መንገደኞች ከሁለት ዓመታት በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ አውስትራሊያ እንዲዘልቁ ተደርጓል።

ወደ አውስትራሊያ ዛሬ ማለዳ 6am ላይ የዘለቁት የመጀመሪያዎቹ ዓለም አቀፍ መንገደኞች ከሎስ አንጀለስ ተነስተው ሲድኒ አውሮፕላን ማረፊያ የደረሱት ሲሆኑ፤ እነሱንም ተከትለው የቶኪዮ፣ ቫንኮቨርና ሲንጋፖር መንገደኞች ሲድኒ ገብተዋል።   

በሚቀጥሉት 24 ሰዓታት ውስጥም 56 ዓለም አቀፍ መንገደኞችን የጫኑ አውሮላኖች የአውስትራሊያ አውሮፕላን ማረፊያዎች ላይ ያርፋሉ፤ በቀጣዮቹ ቀናትም ወደ አውስትራሊያ የሚያቀኑ የዓለም አቀፍ በረራዎች ቁጥር ይጨምራል።

በወረርሽኙ ሳቢያ ዓለም አቀፍ በረራ በመዘጋቱ በየወሩ እስከ $3.6 ኒሊየን ዶላርስ የገቢ እጦት በንግድ ተቋማት ላይ አሳድሯል። 

የዓለም አቀፍ በረራውን መከፈት አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን አንድ ቀን ቀደም ብለው ትናንት እሑድ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ወቅት "የመቆያ ጊዜ አልፏል። ሻንጣዎቻችሁን ሸክፉ። ገንዘቦችቻሁን ይዛችሁ መምጣታችሁን እንዳትዘነጉ፤ በርካታ የምታጠፉባቸው ሥፍራዎች አሉና" ብለዋል። 

የኳንታስ አየር መንገድ ዋና ሥራ አስፈፃሚ አለን ጆይስም በበኩላቸው "ለዚህ የበቃነው ምስጋና ይግባቸውና ክትባቶችን በተከተቡ በሚሊየን የሚቆጠሩ አውስትራሊያውን ምክንያት ነው" በማለት ክትባት የተከተቡ አውስትራሊያውያንን አመስግነዋል። 

ንግሥት ኤልሳቤጥ

ንግሥት ኤልሳቤጥ በኮቪድ-19 ተጠቁ።

የባኪንግሃም ቤተመንግሥት እንዳስታወቀው የ95 ዓመቷ የእንግሊዝ ንግሥት 'መለስተኛ ጉንፋን  መሰል ምልክቶች' የታየባቸው ሲሆን፤ በመጪው ሳምንት ወደ ቀላል ዕለታዊ የሥራ ገበታቸው ይመለሳሉ። 

News
The Queen came to the throne 70 years ago this year when, on February 6 1952, the ailing King George VI - who had lung cancer - died at Sandringham. Source: Press Association

ንግሥቲቱ ባለፈው ሳምንት ከአልጋ ወራሻቸውና በኮቪድ 19 ከተጠቁት የዌልስ ልዑል ቻርልስ ጋር ተገናኝተው ነበር።    

 

 

 


2 min read

Published

Updated

By NACA

Presented by Kassahun Seboqa Negewo


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now