መዲናይቱን አዲስ አበባ ጨምሮ በተለያዩ ክፍለ አገራት የድጋፍና ተቃውሞ ሰልፎች ተካሔዱ

ዩናይትድ ስቴትስ ሰኞ ደቡብ አፍሪካ ላይ በኢትዮጵያ መንግሥትና ሕወሓት መካከል ይካሔዳል ተብሎ የተወጠነውን የሰላም ንግግር እንደምትደግፍ ገለጠች

Demonstration in Addis Ababa, Ethiopia, on October 22, 2022.jpg

Demonstration in Addis Ababa, Ethiopia, on October 22, 2022. - TPLF's authorities said Friday they would attend talks next week to end the war in Ethiopia, as Prime Minister Abiy Ahmed vowed fighting "will end and peace will prevail". Credit: AMANUEL SILESHI/AFP via Getty Images

ዛሬ ቅዳሜ ጥቅምት 12 ቀን 2015 መዲናይቱን አዲስ አበባን ጨምሮ በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍለ አገራት "ለኢትዮጵያ እቆማለሁ፤ ድምፄን አሰማለሁ" በሚል መሪ ቃል የድጋፍና ተቃውሞ ሰልፎች ተካሒደዋል።

በዕለቱ በተካሔዱት ሰልፎች ተሳታፊ የነበሩ ኢትዮጵያውያን "የሰላምና መረጋጋት ጊዜ ደርሷል"፣ "ኢትዮጵያ እንደ አገር እንድትቀጥል መስዋዕትነት የሚከፍለው መከላከያ ሠራዊት ክብር ይገባዋል"፣ የሚሉ መፈክሮችን ከፍ አድርገው በመያዝ ድጋፋቸውን የገለጡ ሲሆን፤ በሌላም በኩል "ኢትዮጵያ ሉ ዓላዊነቷን ለማስከበር የማንም ይሁንታ አያስፈልጋትም" በሚል "ምዕራባውያን ካልተገባ ጣልቃ ገበነት ተቆጠቡ" የሚሉ የተቃውሞ ድምፆችንም አስተጋብተዋል።

በሰልፎቹ ላይ የተለያዩ የመንግሥት ተጠሪዎችና የተቋማት ተወካዮች ተገኝተው ንግግር አሰምተዋል።

የሰላም ንግግር

የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን በአፍሪካ ኅብረት መሪነት በኢትዮጵያ መንግሥትና በትግራይ ክልላዊ አስተዳደር መካከል ደቡብ አፍሪካ ውስጥ የሚካሔደውን የሰላም ንግግር አገራቸው እንደምትደግፍ ትናንት ዓርብ ይፋ ባደረጉት መግለጫ ገለጡ።
አቶ ብሊንከን፤ በሚቀጥለው ሳምንት ሰኞ ደቡብ አፍሪካ ይካሔዳል ተብሎ የሚጠበቀውን የስላም ንግግር አስመልክተው በፍጥነት የተኩስ አቁም እንዲደረግ፣ የኢትዮጵያና ኤርትራ መከላከያ ሠራዊቶችም በአስቸኳይ ከጥምር ማጥቃት ተገትተው ለሰላማዊ ሰዎች ጥበቃ እንዲያደርጉ በማለት ዳግም ጥሪ አቅርበዋል።

ይህ በእንዲህ እንዳለም፤ ሁለቱ የሰላም ንግግር አካሂያጅ ወገኖች ለሰኞው ስብሰባ ነገ እሑድ ቀድመው ደቡብ አፍሪካ ከገቡ የአፍሪካ ኅብረት ባሰናዳው የእራት ግብዣ ላይ ተገናኝተው ይፋዊ ያልሆነ ንግግር እንዲያደርጉ የታሰበ መሆኑን ምንጮች ከወዲሁ ጠቁመዋል።

Share

Published

Updated

By Stringer Report
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service