አውስትራሊያ ውስጥ ለዳግማዊት ንግሥት ኤልሳቤጥ መታሰቢያ ብሔራዊ የሐዘን ሥነ ሥርዓት ተካሔደ

በንግሥቲቲ ሕልፈተ ሕይወት ሳቢያ ለሁለት ሳምንታት የተዘጋው የአውስትራሊያ ፓርላማ በነገው ዕለት የጋራ የሐዘን መግለጫ ለማሳለፍ ልዩ ጉባኤ ይቀመጣል።

Prime Minister Anthony Albanese during the National Memorial Service for Queen Elizabeth II at Parliament House .jpg

Prime Minister Anthony Albanese during the National Memorial Service for Queen Elizabeth II at Parliament House on September 22, 2022 in Canberra, Australia. Credit: Martin Ollman/Getty Images

በ96 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩትን የእንግሊዟን ንግሥትና የአውስትራሊያ ርዕሰ ብሔር ዳግማዊት ኤልሳቤጥን ለመዘከር ዛሬ በአውስትራሊያ ፓርላማ ታላቁ አዳራሽ ውስጥ ብሔራዊ የሐዘን ሥነ ሥርዓት ተካሂዷል።

በልዩ ዝከረ መታሰቢያ ሥነ ሥርዓቱም ላይ ፖለቲከኞች፣ አምባሳደሮችና ሌሎች ተጋባዥ እንግዶች ተገኝተዋል።

በሐዘን ሥነ ሥርዓቱ የአንድ ደቂቃ የሕሊና ተሃስቦ የተካሔደ ሲሆን፤ ጠቅላይ እንደራሴ ዴቪድ ሃርሌይ፣ ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚና የተቃዋሚ ቡድን መሪ ፒተር ዳተን ንግግር አድርገዋል።  

ጠቅላይ እንደራሴ ሃርሌይ "የዛሬዋ ዕለት የሐዘን ቀን ናት። ታሪክ ጥቂት እንደ ንግሥት ኤልሳቤጥ ያሉትን ያወሳል። ስለ ሕልፈተ ሕይወታቸው ስናዝን፤ ከእሳቸውን ድንቅ የሕይወት ትሩፋት ተቋዳሾችና እማኞች በመሆናችንም ውለታ ይገባናል" ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ በበኩላቸው በተለዋዋጩ ዓለም ንግሥቲቱ ለብዙዎች፣ ለረጅም ጊዜያት የዘለቄታ አስተማማኝ እንደነበሩ አንስተዋል።

የተቃዋሚ ቡድ መሪ ፒተር ዳተንም በበኩላቸው" ሐዘን ለፍቅር የሚከፈል ዋጋ ከሆነ፤ ባለፉት 14 ቀናት ውስጥ የመነጨው ሉላዊ ሐዘን ምን ያህል ተፈቃሪ እንደነበሩ የሚናገር ነው" ብለዋል።

በንግሥቲቲ ሕልፈተ ሕይወት ሳቢያ ለሁለት ሳምንታት የተዘጋው የአውስትራሊያ ፓርላማ በነገው ዕለት የጋራ የሐዘን መግለጫ ለማሳለፍ ልዩ ጉባኤ ይቀመጣል።



Share

Published

By Kassahun Seboqa Negewo, NACA
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service