ፊፋ የንግድ ቴሌቪዥን አሰራጪዎች ለሴቶች የዓለም ዋንጫ ውድድር ከ100 ጊዜ ያነሰ የስርጭት ጊዜን በመመደባቸው ትችት ሰነዘረ

ለመጀመሪያ ጊዜ 32 ቡድናት ከጁላይ እስከ ኦገስት የሚሳተፉበት የዓለም ዋንጫ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ከፍተኛ ፍላጎትን ያሳድራል ተብሎ ይጠበቃል።

FIFA President Gianni Infantino.jpg

FIFA President Gianni Infantino says the aim is to break even on the financial cost of running the 2023 Women's World Cup. He says the 2015 and 2019 tournaments made a financial loss. Credit: Getty / Robert Cianflone

የፊፋ ፕሬዚደንት ጂያኒ ኢንፋንቲኖ የቴሌቪዥን አሰራጮች የሴቶች ዓለም ዋንጫን ከወንዶች ለ"100 ጊዜያት ባነሰ" ለማሰራጨት በማሰባቸው ትችት ሰነዘሩ።

ኢንፋኒቶ ቅሬታቸውን ከኦክላንድ ያሰሙት ቅዳሜ ዕለት በአውስትራሊያና ኒውዝላንድ የሚዘጋጀው የሴቶች የዓለም ዋንጫ ምደባ ዕጣ ከመውጣቱ ጥቂት ሰዓታት ቀደም ብለው ነው።
Draw Assistant Maia Jackman draws.jpg
Draw Assistant Maia Jackman draws England during the FIFA Women's World Cup 2023 Final Draw at the Aotea Centre on October 22, 2022 in Auckland, New Zealand. Credit: Harold Cunningham - FIFA/FIFA via Getty Images

የማናቸውንም የቴሌቪዥን ኩባንያዎች ስም ሳይጠቅሱ "አሰራጮች ከወንዶች የዓለም ዋንጫ በ100 ጊዜያት ባነሰ" የስርጭት ሰዓታት ለማስተላለፍ እንደሚሹ ዕቅዶቻቸውን እንዳስታወቋቸው በቅሬታ አመልክተዋል።

አያይዘውም ፊፋ ባለፉት ቅርብ ዓመታት ለሴቶች እግር ኳስ አንድ ቢሊየን ዶላር ወጪ ማድረጉን ገልጠዋል።

በ2015 እና 2019 የሴቶች ዓለም ዋንጫ የፋይናንስ ኪሳራ ያስከተለ ቢሆንም፤ ፊፋ ለመጪው የዓለም ዋንጫ 400 ሚሊየን የአሜሪካን ዶላር ወጪ መድቧል።

ለመጀመሪያ ጊዜ 32 ቡድናት ከጁላይ እስከ ኦገስት የሚሳተፉበት የዓለም ዋንጫ ከመቼውም ጊዜ በበለጠ ከፍተኛ ፍላጎትን ያሳድራል ተብሎ ይጠበቃል።




Share

Published

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service