"ይህ ድል ለመላው ኢትዮጵያ ነው" የ5ሺ ሜትር የወርቅ ሜዳል አሸናፊ ጉዳፍ ፀጋይ

*** ጉዳፍን ተከተለው ኬንያዊቷ ቢትሪስ ቼቤትና ኢትዮጵያዊቷ ዳዊት ስዩም የብርና ነሐስ ሜዳል ባለቤቶች ለመሆን በቅተዋል።

News

Gudaf Tsegay of Team Ethiopia celebrates winning gold in the Women's 5000m Final on day nine of the World Athletics Championships Oregon22. Source: Getty

በኦሪጎን22 የዓለም አትሌቲክስ 5000 ሜትር የሩጫ ውድድር ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ 14 ደቂቃ 46.29 ሰከንዶች በመጨረስ የዓለም ሻምፒዮን ድል አድራጊ ሆና የወርቅ ሜዳል ተሸላሚ ሆናለች።

ጉዳፍን ተከተለው ኬንያዊቷ ቢትሪስ ቼቤት 14 ደቂቃ 46.75 ኢትዮጵያዊቷ ዳዊት ስዩም 14 ደቂቃ 47.36 ሰከንዶች በመጨረስ የብርና ነሐስ ሜዳል ባለቤቶች ለመሆን በቅተዋል። 

News
Silver medalist Beatrice Chebet of Team Kenya, gold medalist Gudaf Tsegay of Team Ethiopia, and bronze medalist Dawit Seyaum of Team Ethiopia. Source: Getty

የኦርጎን22 የ5ሺ ሜትር የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮናዋ ጉዳፍ ውድድሯን በአሸናፊት ከጨረሰች በኋላ ለጋዜጠኞች በሰጠችው ቃለ ምልልስ "በውጤቱ በጣም ደስተኛ ነኝ፤ ይህ ድል ለመላው ኢትዮጵያ ነው" ብላለች። 

የኦሪጎን22 የ10000 ሜትር የወርቅ ሜዳል ባለቤትና የ5000 ሜትር ባለ ክብረወሰኗ ለተሰንበት ግደይ በአምስተኛነት አጠናቅቃለች። 

News
Letesenbet Gidey of Team Ethiopia, gold medalist Gudaf Tsegay of Team Ethiopia, and bronze medalist Dawit Seyaum of Team Ethiopia. Source: Getty

1 min read

Published

By Kassahun Seboqa Negewo


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now