"ይህ ድል ለመላው ኢትዮጵያ ነው" የ5ሺ ሜትር የወርቅ ሜዳል አሸናፊ ጉዳፍ ፀጋይ

*** ጉዳፍን ተከተለው ኬንያዊቷ ቢትሪስ ቼቤትና ኢትዮጵያዊቷ ዳዊት ስዩም የብርና ነሐስ ሜዳል ባለቤቶች ለመሆን በቅተዋል።

News

Gudaf Tsegay of Team Ethiopia celebrates winning gold in the Women's 5000m Final on day nine of the World Athletics Championships Oregon22. Source: Getty

በኦሪጎን22 የዓለም አትሌቲክስ 5000 ሜትር የሩጫ ውድድር ኢትዮጵያዊቷ ጉዳፍ ፀጋይ 14 ደቂቃ 46.29 ሰከንዶች በመጨረስ የዓለም ሻምፒዮን ድል አድራጊ ሆና የወርቅ ሜዳል ተሸላሚ ሆናለች።

ጉዳፍን ተከተለው ኬንያዊቷ ቢትሪስ ቼቤት 14 ደቂቃ 46.75 ኢትዮጵያዊቷ ዳዊት ስዩም 14 ደቂቃ 47.36 ሰከንዶች በመጨረስ የብርና ነሐስ ሜዳል ባለቤቶች ለመሆን በቅተዋል። 
News
Silver medalist Beatrice Chebet of Team Kenya, gold medalist Gudaf Tsegay of Team Ethiopia, and bronze medalist Dawit Seyaum of Team Ethiopia. Source: Getty
የኦርጎን22 የ5ሺ ሜትር የዓለም አትሌቲክስ ሻምፒዮናዋ ጉዳፍ ውድድሯን በአሸናፊት ከጨረሰች በኋላ ለጋዜጠኞች በሰጠችው ቃለ ምልልስ "በውጤቱ በጣም ደስተኛ ነኝ፤ ይህ ድል ለመላው ኢትዮጵያ ነው" ብላለች። 

የኦሪጎን22 የ10000 ሜትር የወርቅ ሜዳል ባለቤትና የ5000 ሜትር ባለ ክብረወሰኗ ለተሰንበት ግደይ በአምስተኛነት አጠናቅቃለች። 
News
Letesenbet Gidey of Team Ethiopia, gold medalist Gudaf Tsegay of Team Ethiopia, and bronze medalist Dawit Seyaum of Team Ethiopia. Source: Getty

Share

Published

By Kassahun Seboqa Negewo

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service