ዛሬ ይፋ በተደረገው የአፍሮ ባሮ ሜትር 8ኛው ዙር የጥናት ውጤት ይፋ መሰረት፤
- ከጥናቱ ተሳታፊዎች 68 በመቶዎቹ ሕገ መንግሥቱ መሻሻል አለበት ያሉ ሲሆን፥ 18 በመቶዎቹ ባለበት ቢቀጥል፤ 11 በመቶ ደግሞ በአዲስ መተካት አለበት ማለታቸውን ጥናቱ አመላክቷል።
- ለፌዴራል መንግስት ተጨማሪ የስራ ቋንቋ ማድረግ/ማካተት በሚለው ላይም ከጥናቱ ተሳታፊዎች ውስጥ 73 በመቶዎቹ ተጨማሪ ሌሎች ቋንቋዎች ቢካተቱ እንደሚስማሙ ሲገልፁ፤ 3 በመቶዎቹ ባለበት እንዲቀጥል ያሉ ሲሆን፥ 24 በመቶዎቹ ደግሞ ተቃውመውታል።
- የጠቅላይ ሚኒስትር የሥልጣን ዘመን በሁለት የምርጫ ጊዜ መገደብን በተመለከተም 68 በመቶዎቹ እንደሚደግፉት፣ 23 በመቶዎቹ እደሚቃወሙ እና 9 በመቶዎቹ ደግሞ ድምጽ አልሰጡበትም።
- ገለልተኛ የሆነ የሕገ መንግሥት ፍርድ ቤት ማቋቋም የሚለውንም 55 በመቶ የደገፉ ሲሆን፥ 25 በመቶ ተቃውመውታል፤ 21 በመቶ ደግሞ ሃሳቡን ድምጽ ሳይሰጡበት ቀርተዋል።

