አብላጫ ኢትዮጵያውያን የሕገ መንግሥት ማሻሻያ እንዲደረግ ይፈልጋሉ - አፍሮባሮ ሜትር

*** የአፍሮ ባሮ ሜትር የጥናት ውጤት

Amharic News August 25, 2020

Source: Courtesy of DK

ዛሬ ይፋ በተደረገው የአፍሮ ባሮ ሜትር 8ኛው ዙር የጥናት ውጤት ይፋ መሰረት፤

 - ከጥናቱ ተሳታፊዎች 68 በመቶዎቹ ሕገ መንግሥቱ መሻሻል አለበት ያሉ ሲሆን፥ 18 በመቶዎቹ ባለበት ቢቀጥል፤ 11 በመቶ ደግሞ በአዲስ መተካት አለበት ማለታቸውን ጥናቱ አመላክቷል።

 - ለፌዴራል መንግስት ተጨማሪ የስራ ቋንቋ ማድረግ/ማካተት በሚለው ላይም ከጥናቱ ተሳታፊዎች ውስጥ 73 በመቶዎቹ ተጨማሪ ሌሎች ቋንቋዎች ቢካተቱ እንደሚስማሙ  ሲገልፁ፤ 3 በመቶዎቹ ባለበት እንዲቀጥል ያሉ ሲሆን፥ 24 በመቶዎቹ ደግሞ ተቃውመውታል።

 - የጠቅላይ ሚኒስትር የሥልጣን ዘመን በሁለት የምርጫ ጊዜ መገደብን በተመለከተም 68 በመቶዎቹ እንደሚደግፉት፣ 23 በመቶዎቹ እደሚቃወሙ እና 9 በመቶዎቹ ደግሞ ድምጽ አልሰጡበትም።

 - ገለልተኛ የሆነ የሕገ መንግሥት ፍርድ ቤት ማቋቋም የሚለውንም 55 በመቶ የደገፉ ሲሆን፥ 25 በመቶ ተቃውመውታል፤ 21 በመቶ ደግሞ ሃሳቡን ድምጽ ሳይሰጡበት ቀርተዋል።


1 min read

Published

By Demeke Kebede


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now