በኮሮናቫይረስ የተጠቁ ሰዎች ቁጥር ከፍ በማለቱ ሳቢያ ሜልበርን ላይ ገደቦች ተጣሉ

*** አውስትራያ የአፍጋኒስታን ኤምባሲዋን ልትዘጋ ነው

SBS Amharic

Source: SBS Amharic

ቪክቶርያ በኮሮናቫይረስ የተጠቁባት ሰዎች ቁጥር ወደ አምስት ከፍ በማለቱ ሜልበርን ላይ ገደቦችን ጥላለች።

ሆኖም ዛሬ ከቀትር በኋላ ተጨማሪ አራት ሰዎች በቫይረሱ መያዛቸውንና በጠቅላላው ወደ ዘጠኝ ከፍ ማለቱን የቪክቶሪያ ዋና የጤና ኃላፊ አስታውቀዋል።

ከዛሬ ሜይ 25 ከምሽቱ 6:00pm ጀምሮ እስከ ጁን 4 ድረስ ጸንቶ በሚቆዩት ገደቦች መሠረት፤

  • በየዕለቱ በመኖሪያ ቤት ውስጥ የመሰባሰብ መጠን በአምስት ሰዎች ተወስኗል
  • በአደባባይ ከ30 ሰዎች መሰባሰብ አይቻልም
  • በተለየ ሕመም ሳቢያ ካልሆነ በስተቀር የሥራ ቦታን ጨምሮ ዕድሜያቸ ከ12 ዓመት በላይ የሆኑ ሁሉ የፊት ጭምብሎችን ማጥለቅ ግድ ይላቸዋል
  • ትምህርት ቤቶችና መሥሪያ ቤቶች ክፍት ሆነው ይቀጥላሉ
  • ከሜልበር ወደ ሪጂናል ቪክቶሪያ ሲጓዙ የገደቦቹን ደንብ መተግበር ይጠበቅብዎታል
  • ከሪጂናል ቪክቶሪያ ወደ ሜልበርን ሲመጡ የገደቦቹን ድንጋጌ መፈጸም ግዴታ ይሆናል።   

ቪክቶሪያ ውስጥ ዘጠኝ የሆቴል ወሸባ ውስጥ ያሉትን ጨምሮ 14 ሰዎች በቫይረሱ ተጠቅተው ይገኛሉ።

ባለፉት 24 ሰዓታት ውስጥ 14,892 ያህል የቪክቶሪያ ነዋሪዎች የኮሮናቫይረስ ምርመራ አካሂደዋል። 

ኤምባሲ አፍጋኒስታን

ዓለም አቀፉ ጦር አፍጋኒስታንን ለቅቆ ለመውጣት በመሰናዶ ላይ ባለበት ወቅት አውስትራሊያ በሚመጡት ጥቂት ቀናት ውስጥ አፍጋኒስታን የሚገኘውን ኤምባሲዋን እንደምዘጋ አስታወቀች።

የኤምባሲውን መዘጋት ተከትሎም በሪጂኑ የሚገኙ የአውስትራሊያ የውጭ ጉዳዮችና ንግድ ዲፓርትመንት ባለሥልጣናት የሥራ ጉብኝቶችን ያደርጋሉ።

የአውስትራሊያን የካቡል ኤምባሲ መዘጋት አስመልክቶ ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን ባወጡት መግለጫ እርምጃው "አውስትራሊያ ከአፍጋኒስታንና ሕዝቧ ጋር መቆሟን አይለውጥም" ብለዋል።   

 

 

 

 


2 min read

Published

Updated

By NACA

Presented by Kassahun Seboqa Negewo


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now