የቀድሞዋ የማይናማር መሪ የአምስት ዓመት እሥራት ተበየነባቸው

*** ሳን ሱ ቺ ለአምስት ዓመታት ካስፈረደባቸው ክስ ባሻገር በሌሎች የተወንጀሉባቸው ክሶቹ ጥፋተኛ ከተባሉ እስከ 100 ዓመታት የሚያስፈርዱባቸው ይሆናሉ።

News

Former Myanmar's State Counsellor Aung San Suu Kyi. Source: Getty

የማያንማር ፍርድ ቤት በጦር ኃይል ከስልጣናቸው ተገፍተው የወረዱትን አንግ ሳን ሱ ቺ ዛሬ ረቡዕ ኤፕሪል 27 በሙስና ተዘፍቀዋል በሚል የአምስት ዓመት እሥራት በየነባቸው።  

በዚህ ዓመት ወርኃ ፌብሪዋሪ ላይ በወታደራዊ መፈንቅለ መንግሥት ከማያንማር መሪነታቸው የተገለሉት የኖቤል ሎሬዬት አንግ ሳን ሱ ሱቺ  በርካታ የወንጀል ክሶች ተመስሮቶባቸዋል። 

ከተመሰረቱባቸው ክሶች መካከል $600,000 ዶላርስ በጥሬ ገንዘብና ወርቅ ጉቦ ተቀብለዋል፣ የምስጢራዊ ድንጋጌዎችን ጥሰዋል፣ የምርጫ ማጭበርበር አካሂደዋል ተብለው ተወንጅለዋል። 

ዛሬ ለአምስት ዓመታት ካስፈረደባቸው ክስ ባሻገር በሌሎች የተወንጀሉባቸው ክሶቹ ጥፋተኛ ከተባሉ እስከ 100 ዓመታት የሚያስፈርዱባቸው ይሆናሉ።

የ76 ዓመቷ የቀድሞዋ የማይንማር መሪ ቀደም ሲልም በጦር ኃይሉ ላይ አሳምፀዋል፣ የኮቪድ-19 ድንጋጌዎችና የቴሌኮሙኒኬሽን ሕግን ጥሰዋል በሚል የስድስት ዓመት የቤት ውስጥ እሥራት ተፈርዶባቸዋል። 

በዛሬው ዕለት ብይን በተበየነባቸው ወቅት ጋዜጠኞች ፍርድ ቤት ተገኝተው ሪፖርት እንዳያቀርቡ የታገዱ ሲሆን፤ የሱ ቺ ጠበቃዎችም ለብዙኃን መገናኛ ጋዜጣዊ መግለጫ እንዳይሰጡ ተከልክለዋል። 

ከመፈንቅለ መንግሥቱ ወዲህ በተነሱ ብጥብጦች ከ1,700 በላይ ሰዎች ሕይወታቸውን እንዳጡና ከ13,000 በላይ ዘብጥያ እንደወረዱ የአካባቢው ዘገባዎች አመልክተዋል። 


1 min read

Published

By NACA

Presented by Kassahun Seboqa Negewo


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now