የአውስትራሊያ ዓመታዊ የዋጋ ግሽበት መጠን ወደ 5.1 ፐርሰንት አሻቀበ

*** የዋጋ ግሽበቱን ለማመጣጠን የአውስትራሊያ ብሔራዊ ባንክ በመጪው ሳምንት የወለድ መጠን ላይ ጭማሪ ሊያደርግ ይችላል

News

Source: SBS

የዋጋ ግሽበት በወርኃ ማርች ሩብ ዓመት ላይ ከተጠበቀው በላይ ንሮ 5.1 ፐርሰንት ደርሷል።

ይህም ካለፈው አንድ አሠርት ዓመት ወዲህ እንዲህ ባለ ፍጥነት ሲያሻቅብ የመጀመሪያው ሆኗል።

የዋጋ ግሽበቱ ወደ  5.1 ያሻቀበው ከዲሴምበር የሩብ ዓመት 2.1 ፐርሰንት ተንስቶ ነው።

ከ2010 ወዲህ ከብሔራዊ ባንክ ከ2 እስከ 3 ፐርሰንት የዋጋ ንረት ግምት በላይ ሲንርም ይህ የመጀመሪያው መሆኑ ነው። 

የነዳጅና የኮንስትራክሽን ዋጋ ጭማሪ ለግሽበቱ ንረት በታካይ አስባብነት ተጠቃሽ ሆነዋል። 

ይህንንም ተከትሎ የብሔራዊ ባንክ ቦርድ በመጪው ሳምንት ማክሰኞ ሲታደም የወለድ መጠኑን አሁን ካለበት 0.1 ፐርሰንት ከፍ ሊያደርግ ይችላል ተብሎ ተገምቷል። 

ከኮቪድ 19 ወረርሽኝ ጋር ተያይዞ የሩስያና ዩክሬይን ጦርነት አውስትራሊያን ጨምሮ በመላው ዓለም የኑሮ ውድነትን አባብሷል።  

የነዳጅ፣ የምግብ ዘይት፣ የግሮሰሪና የእየር ቲኬቶች ዋጋቸው ፈጥኖ ካሻቀቡት ውስጥ ግንባር ቀደም ናቸው።

News
Source: SBS

በቅርቡም በዚህ ዓመት መጨረሻ አውስትራሊያ ውስጥ የአንድ ሲኒ ቡና ዋጋ እስከ $7 ዶላርስ ሊደርስ እንደሚችል የአውስትራሊያ ካፌ ቤቶችና አስተናጋጆች ማኅበር ግምቱን አሳድሯል።

 


1 min read

Published

By NACA

Presented by Kassahun Seboqa Negewo


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now