የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ከሐሙስ አንስቶ መቀሌ በመዝለቅ መደበኛ ኃላፊነቱን መወጣት ይጀምራል

የመከላከያ ሠራዊቱ ግዳጅ አፈፃፀም በፌዴራል መንግሥቱና ሕወሓት መካከል የተደረሰውን የሰላም ስምምነት ተከትሎ ሕገ መንግሥታዊ ኃላፊነቱን የሚወጣ እንደሚሆን ተነግሯል።

Redwan Hussien.jpg

Redwan Hussien, Minister, National Security Advisor to the PM of FDRE. Credit: Erhan Elaldı/Anadolu Agency via Getty Images

የሠራዊቱን ወደ መቀሌ ዘልቆ ግዳጅ ላይ የመሠማራቱን ተግባር በዛሬው ዕለት ይፋ ያደረጉት የኢፌዴሪ ጠቅላይ ሚኒስት ብሔራዊ ደኅንነት አማካሪ አቶ ሬድዋን ሁሴን ናቸው።

አቶ ሬድዋን በኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት አቶ ታገሰ ጫፎ የተመራው ልዑክ ቡድን አባል ሆነው በትናንትናው ዕለት መቀሌ ደርሰው ተመልሰዋል።

የልዑኳን ቡድኑም ከመቀሌ መልስ የጉዟውን ሂደት ለጠቅላይ ሚኒስትሩ ማስረዳቱን የገለጡ ሲሆን፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩም ለተለያዩ የፌዴራል ተቋማት ዋና ሥራ አስፈፃሚዎች ተጀምረው በትግበራ ላይ ያሉ አገልግሎቶች ተፋጥነው እንዲቀጥሉ መመሪያ መስጠታቸውንም አክለው ገልጠዋል።
በመመሪያው መሠረት የኢትዮጵያ አየር መንገድ በነገው ዕለት አቋርጦ የነበረውን የመቀሌ በረራ ለመጀመሪያ ጊዜ የሚቀጥል ሲሆን፤ ሌሎችም አገልግሎት ሰጪዎች የየድርሻ ተግባራቶቻቸውን አፋጥነው የሚቀጥሉ ይሆናል።

Share

Published

By Stringer Report
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service
የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ከሐሙስ አንስቶ መቀሌ በመዝለቅ መደበኛ ኃላፊነቱን መወጣት ይጀምራል | SBS Amharic