የመጀመሪያው የአስትራዜኒካ ኮሮናቫይረስ ክትባት አውስትራሊያ ገባ

*** "የኤርትራ ወታደሮችና የአማራ ክልል ኃይሎች [ከትግራይ] በአስቸኳይ መውጣት አስፈላጊ የመጀመሪያ እርምጃዎች ናቸው" የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ጄ ብሊንኬን

SBS Amharic

Source: SBS Amharic

የመጀመሪያው ዙር 300,000 የአስትራዜኒካ ክትባቶች ጭነት ዛሬ እሑድ ፌብሪዋሪ 28 አውስትራሊያ ገብቷል።

አውስትራሊያ የኦክስፎርድ/አስትራዜኒካ ክትባቶችን ግዢ የፈጸመች ሲሆን 50 ሚሊየኑ ክትባቶች የሚመረቱት አውስትራሊያ ውስጥ ይሆናል። 

Oxford-AstraZeneca
First Doses Of Oxford-AstraZeneca COVID-19 Coronavirus Vaccine Arrive In Australia. Source: Getty

ይህንኑ አስመልክተው ጠቅላይ ሚኒስትር ስኮት ሞሪሰን ሲናገሩ " አያሌ አውስትራሊያውያን የሚከተቡት ኦክስፎርድ/ አስትራዜኒካን ይሆናል። ክትባቶቹን መስጠቱም ማርች 8 ይጀምራል" ብለዋል።

ተከታቢዎች የመጀመሪያውን ክትባት ከተከተቡ በኋላ ሁለተኛውን ክትባት በ12ኛው ሳምንት ይከተባሉ። 

 

ዩናይትድ ስቴትስ ትግራይ

የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ጄ ብሊንኬን ትግራይ ውስጥ እያሽቆለቆለ ያለው የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች ያሳሰባቸው መሆኑንና በበርካታ ቡድናት የተፈጸሙ ግድያዎችን፣ በኃይል ማፈናቀሎችን፣ ወሲባዊ ጥቃቶችን በፅኑ እንደሚያወግዙ ዛሬ ፌብሪዋሪ 28 ባወጡት መግለጫቸው አስታውቀዋል። 

ዩናይትድ ስቴትስ አመፅ እንዲገታ፣ ትግራይ ውስጥ የረድኤት አቅርቦት ለማድረስ ያልተገደበ ሙሉ ተደራሽነት እንዲኖር፣ በሪፖርቶች የተጠቀሱ የሰብ ዓዊ መብቶች ጥሰቶች ሁሉ ገለልተኛ ዓለም አቀፍ ምርመራዎች እንዲካሄድባቸውና ለዚያም የግድ ተጠያቂነት እንዲኖር በተደጋጋሚ ከኢትዮጵያ መንግሥት ጋር መነጋገሯን ገልጠዋል።  

እንዲሁም፤ ዩናይትድ ስቴትስ በኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤትና በውጭ ጉዳዮች ሚኒስቴር በኩል ሙሉዕ የረድኤት አቅርቦት ተደራሽነት እንዲኖር፣ የሰብዓዊ መብቶች ጥሰቶች  ለመመርመርና ሙሉ ተጠያቂነትም እንዲኖር የሚደረግ መሆኑን አስመልክተው ያወጡትን መግለጫ በመልካምነቱ እንደምትቀበለው ጠቁመዋል።

U.S. Secretary of State Antony J. Blinken
U.S. Secretary of State Antony J. Blinken. Source: Getty

ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብም ይህ ዕውን እንዲሆን በጋራ መሥራት እንዳለበት አሳስበዋል። ዩናይትድ ስቴትስ የዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ግቦች እንዲመቱም አብራ እንደምትሠራና የUSAID አደጋ ታዳጊ ግብረ መልስ ቡድን ወደ ኢትዮጵያ እንደሚሄድና በሕይወት መታደግ እገዛዎቹ እንደሚቀጥልም አስታውቀዋል።    

አክለውም "የኤርትራ ወታደሮችና የአማራ ክልል ኃይሎች በአስቸኳይ መውጣት አስፈላጊ የመጀመሪያ እርምጃዎች ናቸው" ብለዋል።

ዓለም አቀፍ ሽርካዎች በተለይም የአፍሪካ ሕብረትና የአካባቢው ወዳጆች፤ የተመድና ሌሎች አካላትንም አካትቶ ትግራይ ውስጥ ያለውን ቀውስ ዕልባት ለማበጀት የግብራዊ ምላሽ ጥሪ አቅርበዋል። 

በማጠቃለያቸውም "ዩናይትድ ስቴትስ ከኢትዮጵያ ሕዝብ ጋር ዘላቂ ወዳጅነት በመገንባት ፀንታ ትቀጥላለች" ብለዋል። 

 


2 min read

Published

Updated

By NACA

Presented by Kassahun Seboqa Negewo


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now