ኳታር የዓለም ዋንጫ ከመጀመሩ በፊት የመንገደኞች የኮቪድ-19 ምርመራን ያስቀረች መሆኑን አስታወቀች

የኳታር ጤና ሚኒስቴር ከኖቬምበር 1 / ጥቅምት 22 አንስቶ መንገደኞች ወደ ኳታር በዘለቁ 24 ሰዓትታ ውስጥ ያደርጉ የነበረው የኮቪድ-19 ምርመራና መንገደኞች ወደ ኳታር ከማቅናታቸው በፊት ከኮቪድ ነፃ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብም የቀረላቸው መሆኑን አስታውቋል።

Visitors take photos with a FIFA World Cup sign in Doha.jpg

Visitors take photos with a FIFA World Cup sign in Doha on October 23, 2022, ahead of the Qatar 2022 FIFA World Cup football tournament. Credit: JEWEL SAMAD/AFP via Getty Images

ይህም የዓለም ዋንጫን ለመመልከት ወደ ዶሃ ለሚያቀኑ የስፖርት አፍቃሪዎች የጤና ዘርፍ ውጣ ውረድ ማቃለያ ተደርጎ በመልካም ጎንነት ተወስዷል።

በኳታር አስተናጋጅነት የሚካሔደው የዓለም ዋንጫ ከኖቬምበር 20 እስከ ዲሴምበር 18 ይከናወናል።

ኳታር ከመካከለኛው ምስራቅ የመጀመሪያዋ የዓለም ዋንጫ አስተናጋጅ አገር ናት።

የዓለም ዋንጫ አስተናጋጇ አገር ውስጥ በቀን 470 ሰዎች ያህል በኮቪድ-19 የሚጠቁ ሲሆን ዕለታዊ የሞት መጠን በአማካይ 0.14 እንደሁ ተመልክቷል።

የአውስትራሊያ እግር ኳስ ቡድን ተጫዋቾችን ጨምሮ የኳታርን ሰብዓዊ መብቶች አያያዝን በተመለከተ ከየአቅጣጫው ብርቱ ትችቶች እየተሰነዘሩባት ይገኛል።

Share

Published

By Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service