ኳታር የዓለም ዋንጫ ከመጀመሩ በፊት የመንገደኞች የኮቪድ-19 ምርመራን ያስቀረች መሆኑን አስታወቀች

የኳታር ጤና ሚኒስቴር ከኖቬምበር 1 / ጥቅምት 22 አንስቶ መንገደኞች ወደ ኳታር በዘለቁ 24 ሰዓትታ ውስጥ ያደርጉ የነበረው የኮቪድ-19 ምርመራና መንገደኞች ወደ ኳታር ከማቅናታቸው በፊት ከኮቪድ ነፃ መሆናቸውን የሚያረጋግጥ ማስረጃ ማቅረብም የቀረላቸው መሆኑን አስታውቋል።

Visitors take photos with a FIFA World Cup sign in Doha.jpg

Visitors take photos with a FIFA World Cup sign in Doha on October 23, 2022, ahead of the Qatar 2022 FIFA World Cup football tournament. Credit: JEWEL SAMAD/AFP via Getty Images

ይህም የዓለም ዋንጫን ለመመልከት ወደ ዶሃ ለሚያቀኑ የስፖርት አፍቃሪዎች የጤና ዘርፍ ውጣ ውረድ ማቃለያ ተደርጎ በመልካም ጎንነት ተወስዷል።

በኳታር አስተናጋጅነት የሚካሔደው የዓለም ዋንጫ ከኖቬምበር 20 እስከ ዲሴምበር 18 ይከናወናል።

ኳታር ከመካከለኛው ምስራቅ የመጀመሪያዋ የዓለም ዋንጫ አስተናጋጅ አገር ናት።

የዓለም ዋንጫ አስተናጋጇ አገር ውስጥ በቀን 470 ሰዎች ያህል በኮቪድ-19 የሚጠቁ ሲሆን ዕለታዊ የሞት መጠን በአማካይ 0.14 እንደሁ ተመልክቷል።

የአውስትራሊያ እግር ኳስ ቡድን ተጫዋቾችን ጨምሮ የኳታርን ሰብዓዊ መብቶች አያያዝን በተመለከተ ከየአቅጣጫው ብርቱ ትችቶች እየተሰነዘሩባት ይገኛል።


1 min read

Published

By Kassahun Seboqa Negewo

Source: SBS



Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now