የነዳጅ ድጎማ ዛሬ እኩለ ለሊት ያበቃል

አሽከርካሪዎች ከነገ ሴፕቴምበር 29 / መስከረም 18 አንስቶ የ25 ሳንቲም የነዳጅ ዋጋ ጭማሪ ያገኛቸዋል።

Fuel excise is set to return on 29 September.jpg

Fuel excise is set to return on 29 September. Credit: AAP

በጊዜያዊነት በመንግሥት ድጎማ ሳቢያ መጠነኛ የዋጋ ቅናሽ ላይ የነበረው የአውስትራሊያ የነዳጅ ዋጋ ዛሬ ረቡዕ እኩለ ለሊት ላይ የድጎማውን ማብቃት ተከትሎ ጭማሪ የሚያሳይ ይሆናል።

ከነገ ሴፕቴምበር 29 / መስከረም 18 አንስቶ የ25 ሳንቲም የዋጋ ጭማሪን ያስከትላል።

የሩስያና ዩክሬን ጦርነት ጋር ተያይዞ አሻቅቦ የነበረውን የነዳጅ ዋጋ ለመቋቋም ያስችል ዘንድ ያለፈው የሞሪሰን መንግሥት እስከ ዛሬ ረቡዕ መስከረም 18 የሚዘልቅና የሚያበቃ የስድስት ወራት ጊዜያዊ የነዳጅ ዋጋ ድጎማ እንዲካሔድ አድርጎ ነበር።

የኑሮ ውድነትን ለመቋቋም እንዲያግዝ የነዳጅ ድጎማው ይቀጥል የሚሉ ድምፆች ቢሰሙም አዲሱ የአልባኒዚ መንግሥት ድጎማው በተቆረጠለት ቀን መስከረም 18 እንዲያበቃ ወስኗል።

በሌላ በኩል ግና የዋጋ ጭማሪው በኒው ሳውዝ ዌይልስና የአውስትራሊያ ካፒታል ቴሪቶሪ ቢያንስ ለአንድ ሳምንት ያህል ያህል የዋጋ ጭማሪ እንደሚያሳይ ተመልክቷል።

የድፍድፍ ነዳጅ ዋጋ ማሽቆልቆልም የነዳጅ የዋጋ ንረት በእጅጉ እንዲያሻቅብ እንደሚአያደርግም ተስፋ አሳድራል።


1 min read

Published

Updated

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo

Source: SBS



Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now