የቀድሞው መከላከያ ሚኒስትር ፒተር ዳተን ያላንዳች ተቀናቃኝ የሊብራል ፓርቲ መሪ ሆነው ተመረጡ።
ፓርቲው የቀድሞዋን የአካባቢ ጥበቃ ሚኒስትር ሱዛን ሊ ያለ ተቀናቃኝ በምክትል መሪነት መርጧል።
የሁለቱን አዲስ የፓርቲ መሪዎች ምርጫ አስመልክቶ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትርና የሊብራል ፓርቲ መሪ ስኮት ሞሪሰን ተመራጮቹ በቂ ተሞክሮ ያላቸው እንደሆኑና ሙሉ ድጋፋቸውንም እንደሚሰጧቸው ተናግረዋል።
በሌላም በኩል የናሽናልስ ፓርቲ ዴቪድ ሊትልፕራውድን በመሪነት ፔሪን ዴቪን በምትል መሪነት መርጧል።

ለናሽናልስ ፓርቲ መሪነት ከሊትልፕራውድ ሌላ በለስ ባይቀናቸውም የቪክቶሪያ ናሽናልስ ምክር ቤት አባል ዳረን ቸስተር የቀድሞውን የፓርቲ መሪና ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተቀናቅነው ለውድድር ቀርበዋል።
አአቶ ዴቪድ ሊትልፕራውድ የናሽናልስ ፓርቲ መሪ ሆነው መመረጣቸውን አስመልክተ ሲናገሩ "በሙያዊ ሕይወታቸው ውስጥ ከፍተኛ ክብር የተሰማቸው ቀን" እንደሆነ ተናግረዋል።
የናሽናልስ ፓርቲ መሪ ምርጫ ከመካሔዱ በፊት ባርናቢ ጆይስ ከቻናል 7 ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ የሊብራል ፓርቲ 19 የምክር ቤት ወንበሮችን ሲያጣ ፓርቲያቸው ግና በእሳቸው አመራር ከአገራዊ ምርጫው በፊት ይዟቸው የነበሩትን የምክር ቤት ወንበሮች ሙሉ በሙሉ እንዳስመረጠ ገልጠዋል።

