ለልጆችና ታዳጊዎች ትኩረት የሰጠው የወዳጅነት ፓርክ ሁለተኛ ፕሮጀክት ተመረቀ

በአዲስ አበባ ከተገነቡት እንጦጦና ወዳጅነት ፓርኮች ብሎም ከአንድነት ፓርክ ቀጥሎ በተለይም ለታዳጊዎችና ልጆች ትኩረት ሰጥቶ የተገነባው የወዳጅነት ፓርክ ሁለተኛው ፕሮጀክት ዛሬ ረፋድ በጠቅላይ ሚኒስትሩ ተመርቋል።

Friendship Park I.jpg

Friendship Park II in Addis Ababa, Ethiopia. Credit: PMOE

ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው፣ የአዲስ አበባ ከተማ ከንቲባ አዳነች አቤቤና ሌሎች የሥራ ኃላፊዎችም በምርቃቱ ተገኝተዋል።

በዚህ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አሕመድ እንደተናገሩት "ህፃናትና ወጣቶች አካላቸውና አዕምሯቸው የሚዳብርበት ስፍራ በመሃል ከተማ ተገንብቷል። እንደ ወዳጅነት ፓርክ ምዕራፍ ሁለት ፕሮጀክት በየክልሉ ለህፃናት የሚሆኑ ሥራዎች ያስፈልጋሉ" ብለዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም "ፓርኩ በውጭ አገራትና በፊልም እናየው የነበረውን ዘመናዊ መዝናኛ እዚሁ አገራችን ላይ ልጆቻችን እንዲጠቀሙበት ያደረገ ነው" ያሉ ሲሆን "መጪው ትውልድ አገሩን እየወደደ እንዲያድግ የሚረዳ ፕሮጀክት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ ተመሳሳይ ፕሮጀክቶችን ከአዲስ አበባ ውጪ በሚገኙ አካባቢዎች ማስፋፋት ያስፈልጋልም" ብለዋል ፡፡

ፓርኩ ስፖርትን፣ ጨዋታንና ማኅበራዊ መስተጋብርን ያቀናጀ ሲሆን ልጆች እየተጫወቱ ሳይንስና ቴክኖሎጂን መለማመድ ያስችላቸዋል።

"ወጣቶች ያነብባሉ፣ ደግሞም ስፖርት ይሠራሉ። ወላጆችና አያቶች ከልጆቻቸው ጋር መጥተው ማኅበራዊ ልምዳቸውን ይለዋወጣሉ። አዲስ ተጋቢዎች በሠርግ ዐጸዱ ጋብቻቸውን ይመሠርታሉ።" ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ "የነገዋ ኢትዮጵያ የተሻለች እንድትሆን የተሻለ ትውልድ እያፈራን እንቀጥላለን"ም ብለዋል።
Friendship Park II.jpg
Adanech Abiebie, Mayor of Addis Ababa (L), Ethiopia's Prime Minister Abiy Ahmed (C), and Zinash Tayachew, First Lady of Ethiopia (R). Credit: PMOE
በዚሁ የፓርኩ ምርቃት አካል በሆነው የወዳጅነት የሠርግ ዐጸድ ላይ በመንግስት ድጋፍ 50 ጥንዶች የጋብቻ ሥነ-ሥርዓታቸውን ያከናውናሉ ተብሎ ይጠበቃል።

ከጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ፊት ለፊት አንስቶ ወደ አሮጌው ቄራ መውረጃና የእሪ በከንቱ አካባቢዎችን ያጠቃለለው ፓርኩ ለአንድ ሳምንት ለጎብኝዎች ክፍት ሆኖ እንደሚቆይም ተገልጿል።

[ደመቀ ከበደ ፡ አዲስ አበባ]

Share

Published

By Demeke Kebede
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service