የቀድሞው የሶቪየት ኅብረት ፕሬዚደንት ሚኻይል ጎርቫቾብ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

የቀዝቃዛውን ጦርነት እንዲያከትም አድርገው ሶቭዬት ኅብረትን ከመበተን መታደግ የተሳናቸው የቀድሞዋ ሶቭየት ኅብረት ፕሬዚደንት ሚኻይል ጎርቫቾቭ በ91 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን የሩሲያ ዜና ኤጀንሲዎች አስታወቁ።

Former Soviet Union president Mikhail Gorbachev has died.jpg

Former Soviet Union president Mikhail Gorbachev has died. Credit: AP / David Longstreath

የመጨረሻው የሶቭዬት ኅብረት ፕሬዚደንት ጎርቫቾቭ ከዩናይትድ ስቴጽ ጋር የጦር መሳሪያዎች ቅነሳና አውሮፓን ለሁለት ከፍሎ የነበረው የበርሊን ግንብ ፈርሶ ሁለቱ ጀርመኖች እንዲዋሃዱና አገራቸውም ከምዕራቡ ዓለም ጋር ለሽርካነት እንድትበቃ አድርገዋል።

የ 'ግላስኖስት' ነፃ ንግግር ፖሊሲያቸውም ቀደም ሲል አይደፈሬ የነበረውን ይሶቭዬት መንግሥትና ኮሙኒስት ፓርቲን ለመተቸት አስችሏል፤ እንዲሁም በቦልቲክ ሪፐብሊኮች ላቲቪያ፣ ሊቱዋኒያ፣ ኢስቶኒያና በሌሎችም ግዛቶች የንገንጠል ጥይቄን ለመቀስቀስ አስችሏል።

Mikhail Gorbachev with the then US president Ronald Reagan.jpg
Mikhail Gorbachev signed a landmark treaty to eliminate intermediate-range missiles with the then US president Ronald Reagan. Credit: AP / Bob Daugherty
 ጎርቫቾቭ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋርከ ታሪካዊው የኑክሊየር ጦር መሣሪያ ቅነሳ ስምምነት ላይ በመድረስና የበርሊን ግንብ ሲፈርስም የሶቪዬትት ጦር እርምጃ እንዳይወስድ ማድረ በማስቻላቸው በ1990 ከፕሬዚደንት ሬገን ጋር የሰላም ኖቤል ሽልማት ተቀብለዋል።



Share

Published

By Kassahun Seboqa Negewo, NACA
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service