የመጨረሻው የሶቭዬት ኅብረት ፕሬዚደንት ጎርቫቾቭ ከዩናይትድ ስቴጽ ጋር የጦር መሳሪያዎች ቅነሳና አውሮፓን ለሁለት ከፍሎ የነበረው የበርሊን ግንብ ፈርሶ ሁለቱ ጀርመኖች እንዲዋሃዱና አገራቸውም ከምዕራቡ ዓለም ጋር ለሽርካነት እንድትበቃ አድርገዋል።
የ 'ግላስኖስት' ነፃ ንግግር ፖሊሲያቸውም ቀደም ሲል አይደፈሬ የነበረውን ይሶቭዬት መንግሥትና ኮሙኒስት ፓርቲን ለመተቸት አስችሏል፤ እንዲሁም በቦልቲክ ሪፐብሊኮች ላቲቪያ፣ ሊቱዋኒያ፣ ኢስቶኒያና በሌሎችም ግዛቶች የንገንጠል ጥይቄን ለመቀስቀስ አስችሏል።

ጎርቫቾቭ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋርከ ታሪካዊው የኑክሊየር ጦር መሣሪያ ቅነሳ ስምምነት ላይ በመድረስና የበርሊን ግንብ ሲፈርስም የሶቪዬትት ጦር እርምጃ እንዳይወስድ ማድረ በማስቻላቸው በ1990 ከፕሬዚደንት ሬገን ጋር የሰላም ኖቤል ሽልማት ተቀብለዋል።

