የኮቪድ - 19 ወሸባ መቆያ ከሰባት ወደ አምስት ቀናት ዝቅ እንዲል የአውስትራሊያ ብሔራዊ ካቢኔ ወሰነ

በአገር ውስጥ በረራ የፊት ጭምብል የማጥለቅ ግዴታም ተነስቷል።

Anthony Albanese, Australia's prime minister.jpg

Anthony Albanese, Australia's prime minister, speaks during an event at the National Press Club in Canberra, Australia, on Monday, Aug. 29, 2022. Credit: Hilary Wardhaugh/Bloomberg via Getty Images

ዛሬ ኦገስት 31 / ነሐሴ 25 የአውስትራሊያ ብሔራዊ ካቢኔ ባካሔደው ስብሰባ የኮቪድ - 19 ወረርሽኝ ወሸባ ገብቶ የመቆያ ጊዜ ከሰባት ቀናት ወደ አምስት ቀናት ዝቅ እንዲል ወስኗል።

 ቀደም ሲል በአገር ውስጥ በረራ ወቅት የፊት ጭምብል ማጥለቅ ግዴታ ተነስቷል።

የወሸባ ቆይታው ጊዜ ከሰባት ወደ አምስት ቀናት ዝቅ ማለት አውስትራሊያን ከዩናይትድ ስቴትስና ካናዳ የወሸባ ጊዜ ገደቦች ጋር ተመሳሳይ የጤና መርህ ላይ ያካትታታል።

አዲሱ የወሸባ ቆይታ ጊዜና በአገር ውስጥ በረራ ወቅት የፊት ጭምብል ያለማጥለቁ ድንጋጌ ግብር ላይ የሚውለው ከሴፕቴምበር 9 / ጳጉሜን 4 ጀምሮ ነው።

 

ምንም እንኳ የድንጋጌ ለውጥ ቢደረግም ሰዎች ኃላፊነት በተመላው መንገድ ጥንቃቄዎችን ከማድረግ ወደ ኋላ እንዳይሉና የሰባት ቀናት የወሸባ ቆይታው አሁንም በአረጋውያን ክብካቤ፣ የግብረ አካል ጉዳተኞች ክብካቤና የቤት ውስጥ ክብካቤ ሠራተኞች ላይ የፀና እንደሚሆን ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ ገልጠዋል።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ አክለውም፤ የወርረሽኝ የቤት ውስጥ ቆይታ ክፍያን አስመልክቶ ለመምከርና ከውሳኔ ላይ ለመድረስ ብሔራዊ ካቢኔው ከሁለት ሳምንታት በኋላ ዳግም እንደሚገናኝ አስታውቀዋል።


Share

1 min read

Published

By NACA, Kassahun Seboqa Negewo

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now