የጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ ሌበር ፓርቲ ራሱን ችሎ መንግሥት ማቆም የሚያስችሉት 76 የምክር ቤት ወንበሮችን አገኘ።
ለመጀመሪያ ጊዜ የታደመው የሌበር ፓርቲ ፌዴራል ምክር ቤት የግራና ቀኝ አንጃ ጠቅላይ ሚኒስትር አልባኒዚ ወደ ስብሰባው አዳራሽ ሲገቡ ሞቅ ባለ ጭብጨባ ተቀብሏቸዋል።
አቶ አልባኒዚ ከሁለተኛው የዓለም ጦርነት በኋላ ፓርቲያቸውን ከተቃዋሚነት ለመንግሥትነት ያበቁ አራተኛው ጠቅላይ ሚኒስትር ናቸው።
የሌበር መንግሥት ለማቆም የሚያስችለውን 76 የምክር ቤት ወንበሮች ድል አድርጎ ያገኘ ቢሆንም ጊልሞርን አሸንፎ 77ኛውን የምክር ቤት ወንበር ለማግኘት እየመራ ይገኛል።
ጠቅላይ ሚኒስትሩ ዛሬ ማክሰኞ ከቀትር በፊት ካንብራ ለታደሙት የሌበር ፌዴራል ምክር ቤት አባላት ባደረጉት ንግግር ፓርቲያቸው እንደ መንግሥት አንድም በከንቱ የሚያጠፋው ቀን እንደማይኖር አመላክተዋል።

አያይዘውም፤ መንግሥታቸው የሠራተኞችን ደኅንነት ለማስጠበቅ፣ የኑሮ ውድነትን ለመቀነስ፣ የአረጋውያን ክብካቤን ለማሻሻል፣ ማምረቻዎችን በስፋት አምራች ለማድረኛ የአየር ንብረት ለውጥ ጦርነት እንዲያከትም የሚያደርግ መሆኑን አስታውቀዋል።
የነባር ዜጎች የፓርላማ ድምፅና የፀረ ሙስና ኮሚሽን መቋቋም በዚህ ዓመት ውስጥ ዕውን እንደሚሆን ገልጠዋል።
47ኛው የአውስትራሊያ ፓርላማም ጁላይ 26 / ሐምሌ 19 እንደሚከፈት ተናግረዋል።

