የኢትዮጵያ መንግሥት የቆቦ ከተማን ለመልቀቅ ግድ መሰኘቱን ገለጠ

የሕወሓት ጦር ቆቦ መድረሱ ተነገረ

on the road to Kobo, on the border with Tigray, a 155-millimeter gun bombed by a drone of the Ethiopian government .jpg

on the road to Kobo, on the border with Tigray, a 155-millimeter gun bombed by a drone of the Ethiopian government፣ on January 19, 2022. Credit: Alvaro Canovas/Paris Match via Getty Images

የኢትዮጵያ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ኦገስት 27, 2022 / ነሐሴ 21, 2014 ባወጣው መግለጫ ሕወሓት የሰው ኃይል ማዕበል በመጠቀም የቆቦ ከተማን በበርካታ አቅጣጫ እያጠቃ መሆኑንና ሠርጎ ገቦችንም በማሥረግ የከተማ ውስጥ ውጊያ ለማድረግ የሚያስችል ሁኔታ እየፈጠረ እንደሚገኝ አመላክቷል።

አያይዞም፤ ይህንኑ ምክንያት በማድረግ "የሕዝብን ከፍተኛ ፍጅት ለማስወገድ ሲባል የመከላከያ ኃይል የቆቦ ከተማን በመልቀቅ እና ወደ ኋላ መጥቶ ለመከላከል የሚያስችለውን ወታደራዊ ይዞታዎችን ለመያዝ ተገዷል" ሲል አስታውቋል።

ሆኖም ሕወሓት "በሕዝብ ማዕበል ማጥቃቱን ካላቆመ መከላከያ ሕጋዊ፣ ሞራላዊና ታሪካዊ ግዴታውን ለመወጣት የሚገደድ ይሆናል" በማለት የመንግሥትን ቀጣይ እርምጃ አመላክቷል።

ይህ በእንዲህ እንዳለም፤ በትግራይ የብዙሃን መገናኛ በኩል ባለፉት ሶስት ተከታታይ ቀናት የተካሔዱ ውጊያዎችን ተከትሎ ቆቦ ከተማን በማከል ጉጉዶ፣ ፎኪሳ፣ ዞብል፣ መንደፈራ፣ ሮቢት፣ ሺህዎች ማርያምና ተኩለሽ በሕወሓት ጦር ቁጥጥር ስር ለመሆን መብቃታቸው ተዘግቧል።

ዘገባውን አስመልክቶ በመንግሥትም ሆነ በሌሎች ምንጮች ማረጋገጫ አልተሰጠም።


1 min read

Published

By Stringer Report

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now