የኢትዮጵያ መንግሥት የቆቦ ከተማን ለመልቀቅ ግድ መሰኘቱን ገለጠ

የሕወሓት ጦር ቆቦ መድረሱ ተነገረ

on the road to Kobo, on the border with Tigray, a 155-millimeter gun bombed by a drone of the Ethiopian government .jpg

on the road to Kobo, on the border with Tigray, a 155-millimeter gun bombed by a drone of the Ethiopian government፣ on January 19, 2022. Credit: Alvaro Canovas/Paris Match via Getty Images

የኢትዮጵያ መንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት ኦገስት 27, 2022 / ነሐሴ 21, 2014 ባወጣው መግለጫ ሕወሓት የሰው ኃይል ማዕበል በመጠቀም የቆቦ ከተማን በበርካታ አቅጣጫ እያጠቃ መሆኑንና ሠርጎ ገቦችንም በማሥረግ የከተማ ውስጥ ውጊያ ለማድረግ የሚያስችል ሁኔታ እየፈጠረ እንደሚገኝ አመላክቷል።

አያይዞም፤ ይህንኑ ምክንያት በማድረግ "የሕዝብን ከፍተኛ ፍጅት ለማስወገድ ሲባል የመከላከያ ኃይል የቆቦ ከተማን በመልቀቅ እና ወደ ኋላ መጥቶ ለመከላከል የሚያስችለውን ወታደራዊ ይዞታዎችን ለመያዝ ተገዷል" ሲል አስታውቋል።

ሆኖም ሕወሓት "በሕዝብ ማዕበል ማጥቃቱን ካላቆመ መከላከያ ሕጋዊ፣ ሞራላዊና ታሪካዊ ግዴታውን ለመወጣት የሚገደድ ይሆናል" በማለት የመንግሥትን ቀጣይ እርምጃ አመላክቷል።


ይህ በእንዲህ እንዳለም፤ በትግራይ የብዙሃን መገናኛ በኩል ባለፉት ሶስት ተከታታይ ቀናት የተካሔዱ ውጊያዎችን ተከትሎ ቆቦ ከተማን በማከል ጉጉዶ፣ ፎኪሳ፣ ዞብል፣ መንደፈራ፣ ሮቢት፣ ሺህዎች ማርያምና ተኩለሽ በሕወሓት ጦር ቁጥጥር ስር ለመሆን መብቃታቸው ተዘግቧል።

ዘገባውን አስመልክቶ በመንግሥትም ሆነ በሌሎች ምንጮች ማረጋገጫ አልተሰጠም።

Share

Published

By Stringer Report
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service