ወላይታ ዞን አዲስ አስተዳዳሪ ሾመ

*** የወላይታ ዞን ምክር ቤት

Wolayta

Dr Endrias Geta Source: Supplied

የወላይታ ዞን ምክር ቤት  ዛሬ ባደረገው ስብሰባ ዶክተር እንድሪያስ ጌታን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አድርጎ መሾሙን አልዓይን ዘግቧል፡፡

የደቡብ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ዶ/ር እንድሪያስ በዞንና በክልል ደረጃ በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች መስራታቸው በሹመቱ ወቅት ተገልጿል፡፡ 

የቀድሞው የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳጋቶ ኮምቤ “ከብልጽግና ፓርቲ ሥነ ምግባር በወጣ መንገድ  ህዝብና መንግስት የሰጣቸውን ኃላፊነት ወደ ጎን በማለት ለውጡን ለመቀልበስ በውስጥና በውጭ ከሚንቀሳቀሱ አካላት ጋር ተቀናጅተው እየሰሩ እንዳለ ደርሼበታለሁ” በማለት የፓርቲው የደቡብ ቅርንጫፍ አቶ ዳጋቶን ሰሞኑን ከኃላፊት ማንሳቱ ይታወሳል፡፡


1 min read

Published

By Demeke Kebede


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now