የወላይታ ዞን ምክር ቤት ዛሬ ባደረገው ስብሰባ ዶክተር እንድሪያስ ጌታን የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አድርጎ መሾሙን አልዓይን ዘግቧል፡፡
የደቡብ ግብርና ምርምር ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር የነበሩት ዶ/ር እንድሪያስ በዞንና በክልል ደረጃ በተለያዩ የኃላፊነት ቦታዎች መስራታቸው በሹመቱ ወቅት ተገልጿል፡፡
የቀድሞው የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ዳጋቶ ኮምቤ “ከብልጽግና ፓርቲ ሥነ ምግባር በወጣ መንገድ ህዝብና መንግስት የሰጣቸውን ኃላፊነት ወደ ጎን በማለት ለውጡን ለመቀልበስ በውስጥና በውጭ ከሚንቀሳቀሱ አካላት ጋር ተቀናጅተው እየሰሩ እንዳለ ደርሼበታለሁ” በማለት የፓርቲው የደቡብ ቅርንጫፍ አቶ ዳጋቶን ሰሞኑን ከኃላፊት ማንሳቱ ይታወሳል፡፡
Share

