ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ በመጀመሪያ ዓለም አቀፍ ጉዟቸው በቶኪዮ አራትዮሽ ጉባኤ ላይ ተገኙ

*** የቻይና ጠቅላይ ሚኒስትር ለዲሱ የአውስትራሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ የእንኳን ደስ ያለዎት መልዕክት አስተላለፉ፤ የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሰለሞን ደሴቶችንና ስድስት የፓስፊክ አገራትን ከሐሙስ ጀምረው ሊጎበኙ ነው።

News

The four 'Quad' leaders in Tokyo. Source: AAP

አዲሱ የአውስትራሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ ቃለ መሃላ ከፈፀሙ ጥቂት ሰዓታት በኋላ ትንናት ወደ ቶኪዮ አምርተው ዛሬ ቶኪዮ ላይ በተካሔደው የአራትዮሽ የፀጥታ መድረክ ጉባኤ ላይ ታድመዋል።

 

አውስትራሊያን ጨምሮ የመድረኩ ታዳሚዎች፤ የዩናይትድ ስቴትስ፣ ጃፓንና ሕንድ መሪዎች ናቸው። 

 

በመሪዎቹ የአንድ ቀን ጉባኤ ላይ አራቱ አገራት የቻይናን የኢንዶ ፓስፊክ ተፅዕኖ ለመቀነስ በይበልጥ ተቀራርበው መሥራት እንዳለባቸው በአቶ አልባኒዚ በኩል ማሳሰቢያ ቀርቧል። 

News
Australian Prime Minister Anthony Albanese attends the Quad Leaders’ summit on May 24, 2022 in Tokyo, Japan. Source: Getty

አቶ አልባኒዚ ያለፈው የሞሪሰን መንግሥት ከቻይና ጋር ግጭት ሊፈጠር እንደሚችል ደጋግሞ ሲያነሳ ስለበረው የፀጥታ ጉዳይ በጋዜጠኞች ተጠይቀው ሲመልሱ " በቀጣናው የምንሻው ሰላምና መረጋጋትን ነው። ያንንም ተገቢ በሆነ ዲፕሎማሲያዊ ሂደት ቀጣናዊ ግንኙነትን መገንባት ነው" ብለዋል።  

 

ይህ በእንዲህ እንዳለም፤ የቻይና ጠቅላይ ሚኒስትር ለአዲሱ ተመራጭ የአውስትራሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር የእንኳን ደስ ያለዎት መልዕክት አስተላልፈዋል። 

 

በመልዕክታቸው ላይም አያይዘው "ቻይና ያለፈውን ወደ ኋላ ትታ ወደፊት በመመልከት፣ እኩል መከባበርና የጋራ ትሩፋት መርሆችን በመመርኮዝ፣ የቻይና አውስትራሊያ ስትራቴጂያዊ ወዳጅነን ያካተተ የሰከነ ልማትን ከፍ በማድረግ ከአዲሱ የአውስትራሊያ መንግሥት ጋር ለመሥራት ትሻለች" ብለዋል። 

 

በሌላም በኩል በቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዋንግ ሊ የሚመራ ከፍተኛ ልዑክ ቡድን ሰለሞን ደሴቶችን ጨምሮ ስድስት የፓስፊክ አገራትን ይጎበኛል። 

News
Chinese Foreign Minister Wang Yi will lead a delegation to PNG and other Pacific nations. Source: AAP

ጉብኝቱን አስመልክቶ የሰለሞን ደሴቶች ጠቅላይ ሚኒስትር ሶጋቫሬ አገራቸው "ከቻይና ጋር የምታደርገው የልማት ወዳጅነት በታሪካችን ውስጥ በጣሙን ወሳኝ ነው" ብለዋል።  

 

የቻይና ልዑክ ቡድን የፓስፊክ አገራቱን ከሐሙስ እስከ ቅዳሜ ባሉት ቀናት ውስጥ ቀጣናዊ ጉብኝት ያካሒዳል። 


2 min read

Published

Updated

By NACA

Presented by Kassahun Seboqa Negewo


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now