ዲዬጎ ማራዶና በዓለም የእግር ኳስ ታሪክ ከሕይወት በላይ ግዘፍ ነስቶ በስፖርቱ ዓለም አንጸባራቂ አሻራውን ትቶ በ60 ዓመቱ ያለፈው ረቡዕ ዕለት ከቦነስ አይረስ ከተማ ፈንጠር ብሎ ባለው ቤቱ በልብ ድካም ሕመም ነው።
ማራዶና በቅርቡ በነበሩበት የጤና ችግሮች ሳቢያ አስቸኳይ ቀዶ ሕክምና ለማድረግ ግድ ተሰኝቶ ነበር።
የአርጀንቲና ፕሬዚደንት አልቤርቶ ፈርናንዴዝ ታላቅ የእግር ኳስ ኮከብ የነበረውን ማራዶናን ክብር ለመቸር የሶስት ቀናት ብሔራዊ የኃዘን ቀን አውጀዋል።
የአርጀንቲና እግር ኳስ ማኅበርም በበኩሉ የተሰማውን ጥልቅ ኃዘን ገልጦ "ዲዬጎ አርማንዶ ማራዶና ሁሌም ልባችን ውስጥ ትኖራለህ" ሲል ልባዊ ከበሬታና ፍቅሩን ገልጧል።
ማራዶና የትውልድ አገሩን አርጀንቲና ለ1986ቱ የዓለም እግር ኳስ ዋንጫ ድል አብቅቷል።
እንዲሁም በ1990 የአርጀንቲና ብሔራዊ እግር ኳስ ቡድን ጣሊያን ላይ ለፍጻሜ ግጥሚያ አድርሷል በ2010ሩ የደቡብ አፍሪካ የዓለም ዋንጫም የመሪነት ሚና ተጫውቷል።
ብራዚሊያዊው ታላቁ የእግር ኳስ ኮከብ ፔሌም "እኔ ውድ ጓደኛዬን፤ ዓለም እጅግ ዝነኛ ሰውን አጥቷል" ሲል ኃዘኑን ገልጧል።
ፕሬዚደንት ፈርናንዴዝም በበኩላቸው " ከዓለም ታላቅ ከፍታ ላይ አድርሰኸናል፤ በእጅጉም ደስተኞች አድርገኸናል"
"አንተ የታላላቆች ሁሉ ታላቅ ነበርክ። ከእኛ ጋር በመሆንህ እናመሰግንሃልን። በሕይወት ዘመናችን ሁሉ በናፍቆት እናስብሃለን" ሲሉ፤
ናፖሊ "ዲዬጎ - ለዘላለሙ ቻዎ!" ብሏል።

