በዚህ ሳምንት ውስጥ ከቅኝ ግዛት ታርኳ ተላቅቃ የዓለም አዲሲቱ ሪፐብሊክ ለመሆን የበቃቸው ባርቤዶስ አውስትራሊያ ውስጥ የሪፕበሊክ ጉዳይ ዳግም የመነጋገሪያ አጀንዳ ሆኖ እንዲነሳ አድርጓል።
የባርቤዶስ ሪፐብሊክ ምሥረታ አውስትራሊያን ጨምሮ በመላው ዓለም በእንግሊዝ ሕገ መንግሥታዊ የዘውድ ፓርላማ አስተዳደር ስር ባሉ አገራት ዘንድ ቀልብ ስቦ መነጋገሪያ ለመሆን በቅቷል።
የብሔራዊ አውስትራሊያ ሪፕብሊክ ንቅናቄ ዳይሬክተር ሳንዲ ቢያር የባርቤዶስን እርማጃ የሚያደንቁና በምሳሌነትም የሚመለከቱት መሆኑን ገልጠዋል።
አያይዘውም “አውስትራሊያ በተመሳሳይ መልኩ በተቻለ ፍጥነት ሪፐብሊክ ስትሆን ማየት እንሻለን። ዳግማዊት ንግሥት ኤልሳቤጥ ዙፋን ላይ እያሉ ሪፑብሊክ መሆንን እንወዳልን። ለግልጋሎታቸውም በሕይወት ሳሉ ሙሉ ነፃ አገር በማቆም ማምስገን እንሻለን" ብለዋል።
ላሊበላ
የመከላከያ ሰራዊት፣ የአማራ ልዩ ኃይል፣ ሚሊሺያ እና ፋኖ የላሊበላ ከተማን እና የላሊበላ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያን መቆጣጠራቸውን የመንግስት የኮሚዩኒኬሽን አገልግሎት ምሽቱን አስታውቋል።
የመንግስት ኮሙኒኬሽን አገልግሎቱ እንዳለው ጥምር ሃይሎቹ የሰቆጣ ከተማን ለመቆጣጠር በግስጋሴ ላይ ይገኛሉ ሲልም ገልጿል።
ሚኒስትሩ ዶር ለገሰ ቱሉ ረቡዕ ረፋድ ላይ በሰጡት መግለጫ የመከላከያ ሰራዊት፣ የአማራ ልዩ ኃይልና ፋኖ በጋሸና ግንባር በርካታ አካባቢዎችን መቆጣጠሩን አስታውቀው ነበር።
በሕወሓት በኩል እስካሁን የመንግሥትን መግለጫ አስመልክቶ ይፋ መግለጫ አልወጣም።

