የኮሮናቫይረስ ወረርሽኝን ለመከላከል ከተጣሉት ገደቦች ጋር ተያይዞ የአውስትራሊያ ሥራ አጥነት ቁጥር በወርኃ ጁን ውስጥ 7.4 ደርሷል።
በዚሁ ጁን ወር ውስጥ 69,300 ሥራዎች ሲታጠፉ 210,800 ሰዎች ለቅጥር በቅተዋል።
የአውስትራሊያ ስታቲስቲክስ ቢሮ ዛሬ ሐሙስ ይፋ እንዳደረገው የግማሽ ቀን ሥራ በ 249,000 ከፍ ሲል፤ የሙሉ ቀን ሥራ በ 38,100 ዝቅ ብሏል።
የሥራ አጥነት ቁጥር በወርኃ ኤፕሪል ከነበረበት 6.4 ፐርሰንት በወርኃ ሜይ ወደ 7.1 ከፍ ማለቱ የሚያመለከተው በማርች መጨረሻ ግድም የማኅበራዊ ርቀት መመሪያዎችን ለማስጠበቅ የተወሰዱት እርምጃዎች ተፅዕኖ እንደሆነም ተገልጧል።
የደቡብ አውስትራሊያ ሥራ አጥነት ቁጥር 8.8 ፐርሰንት፣ ምዕራብ አውስትራሊያ 8.7 ፐርሰንት፣ ኩዊንስላንድ 7.7 ፐርሰንት፣ የቪክቶሪያ ሥራጥነት ቁጥር 7.5 ፐርሰንት ላይ ሲረጋ፤ የኒው ሳውዝ ዌይልስ ሥራ አጥነት ወደ 6.9 ወርዷል።

