የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት አክሱምንና አድዋን ሙሉ በሙሉ እንዲሁም የአዲግራትን ዙሪያ መቆጣጠሩን የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የመረጃ ማጣሪያ በኅዳር 11- 2013 መግለጫው አስታወቀ፡፡
በመገለጭው ላይ እንደሠፈረው በምዕራብ ግንባር የሕወሓት ኃይልን እያጠቃ ያለው የመከላከያ ሠራዊት፣ ከሽሬ በኋላ ሰለህለሃ ላይ የመሸገ የሕወሓት ኃይል ገጥሞት እንደነበርና ሆኖም የተከላካይ ኃይሉን ሰብሮ በመግባት አክሱምን ሙሉ በሙሉ መቆጣጠር መቻሉን ገልጧል።
አያይዞም የመከላከያ ሠራዊቱ እንቲጮንና የአዲግራትን ዙሪያ ተቆጣጥሮ ወደ አዲግራት ከተማ እያመራ እንደሚገኝ አመላክቷል።
በሕወሓት በኩል የአክሱምና አድዋ ከተሞችን መያዝ አስመልክቶ ለለጊዜው ማስተባበያም ሆነ ማረጋገጫ አልተደመጠም።

