የኒው ሳውዝ ዌይልስ በጅሮንድና ምክትል የሊብራል ፓርቲ መሪ ዶሚኒክ ፔሮቴይ የኒው ሳውዝ ዌይልስ እንደራሴ ለመሆን እጃቸውን አውጥተዋል።
የምዕራብ ሲድኒ የምክር ቤት አባል ስቱዋርት ኤይሬስም በበኩላቸው ለምክትል መሪነት እንደሚወዳደሩ አስታውቀዋል።
የፕላን ሚኒስትር ሮብ ስቶክስ ዓርብ ዕለት ከእንደራሴነታቸው የለቀቁትን ግላዲስ በርጂክሊያን ለመተካት በተቀናቃኝነት ተነስተዋል።
በወ/ሮ በርጂክሊያን ምትክ አዲስ እንደራሴ ለመተካት የኒው ሳውዝ ዌይልስ ሊብራል ፓርቲ የምርጫ ሥነ ስር ዓቱን ማክሰኞ ኦክቶበር 5 ያካሂዳል።
Share

