በኮቨድ - 19 የተጠቁት ፕሬዚደንት ትራምፕ ለሕክምና ወደ ወታደራዊ ሆስፒታል ተወሰዱ

*** ምክትል ፕሬዘደንት ማይክ ፔንስና የዲሞክራት ዕጩ ፕሬዚደንት ጆ ባይደን በኮሮናቫይረስ አልተያዙም

Donald Trump

Donald Trump walks along the South Lawn of the White House before boarding Marine One. Source: AAP / Michael Nigro

በኮሮናቫይረስ የተጠቁት የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ከዋሽንግተን ወጣ ብሎ ሜሪላንድ ወደ ሚገኘው ዎልተር ሪድ ወታደራዊ የሕክምና ማዕከል በማሪን  ዋን ሔሊኮፕተር ተወስደዋል።

የዋይት ሃውስ ቃል አቀባይ ካይሊ ማክኢናኒ "በሐኪማቸውና በሕክምና ኤክስፐርቶች ምክረ ሃሳብ መሠረት  ፕሬዚደንቱ ለሚቀጥሉት ጥቂት ቀናት ዎልተር ሪድ ከሚገኘው ፕሬዚደንታዊ ጽሕፈት ቤት ሆነው ይሠራሉ" በማለት ተናግረዋል።
Trump
Marine One lifts off from the White House to carry President Donald Trump to Walter Reed National Military Medical Center Source: AP


ፕሬዚደንት ትራምፕ ወደ ሆስፒታል ከመሄዳቸው በፊት ቀርጸው ባስተላለፉት አጭር ቪዲዮ "ደህና ነኝ። የላቀ ድጋፋቸውን የቸሩኝን ሁሉ ላመሰግን እሻለሁ" ብለዋል።

የዲሞክራት ዕጩ ፕሬዚደንት ጆ ባይደንና ዕጩ ምክትል ፕሬዚደንት ካማላ ሃሪስ የኮሮናቫይረስ ምርመራ ከነባለቤቶቻቸው አካሂደው ከቫይረሱ ነጻ መሆናቸው ታውቋል።

የዩናይትድ ስቴትስ ምክትል ፕሬዚደንት ማይክ ፔንስና ባለቤታቸውም እንዲሁ ምርመራ ተደርጎላቸው ከቫይረሱ ነጻ ሆነው ተገኝተዋል።

ምርምራ ካካሄዱ በፕሬዚደንቱ አካባቢ የነበሩ የቅርብ ረዳቶችና የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት አባላት ውስጥ እስካሁን ስድስቱ በቫይረሱ መያዛቸው ተገልጧል። 


Share

1 min read

Published

Updated

By NACA


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service