" ቁጥራቸው 27 የሆኑ ተለማማጅ ሐኪሞችና 2 ከፍተኛ ሐኪሞች በኮቪድ - 19 ተይዘውብናል" - ዶ/ር አሥራት አጸደወይን

*** ጎንደር ዩኒቨርሲቲ

COVID - 19 Ethiopia

Asrat Atsedewoin (PhD), President of the University of Gondar Source: Supplied

ለጎንደር ከተማና አጎራባች አካባቢዎች ህክምና በመስጠት በሚታወቀው በጎንደር ዩኒቨርሲቲ ሪፈራል ሆስፒታልና ሕክምናና ጤና ሳይንስ ኮሌጅ የሚሰሩ ሁለት ከፍተኛ ሐኪሞችና 27 ተለማማጅ ሐኪሞች (Interns) በኮሮናቫይረስ መያዛቸው መረጋገጡን የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝደንት ዶ/ር አሥራት አጸደወይን ለSBS አውስትራሊያ ገልፀዋል።

ይህንን ተከትሎም ዩኒቨርሲቲ ሆስፒታሉ ለእነዚህ ባለሙያዎች አስፈላጊውን ክትትልና ድጋፍ እያደረገላቸው ነው ብለዋል።

"ተጋላጭ የሆኑበት ምክንያት ምንድን ነው?" በሚል ላቀረብናላቸው ጥያቄ ሲመልሱ  " በኮቪድ 19 ከተያዙት መካከል አዲስ አበባ ደርሰው የተመለሱ በመኖራቸው መነሻው ይህ ሊሆን ይችላል" የሚል ጥርጣሬ እንዳላቸው ገልፀው "ይሁንና ዋናው ምክንያት እያጣራን ነው" ብለዋል።

ዶ/ር አሥራት ጨምረው እንደተናገሩት "የሕክምና ሥራ በባህሪው አጋላጭ እንደመሆኑ ሆስፒታሉ በፌደራል ጤና ጥበቃ ሚኒስቴር ባስቀመጠው መመሪያ መሰረት የተጋላጭነት መከላከያ ቁሳቁሶችን ሲያቀርብ ነበር ፤ አሁንም እያቀረበ ነው " ሲሉ አስረድተዋል።

"የሆስፒታሉና የጤናና ሕክምና ሳይንስ ኮሌጁ ማኅበረሰብ በተፈጠረው አጋጣሚ ሳይደናገጥ ሕብረተሰቡን ማገልገሉን እንደቀጠለ ነው፤ ስርጭቱን ለመቀነስም እየሰራን ነው" ብለዋል ዶ/ር አሥራት።


1 min read

Published


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now