የኮቪድ-19 ወቅታዊ መረጃ፤ የመጀመሪያ ዙር ክትባት የተከተቡ አውስትራሊያውያን ቁጥር ዛሬ ከ90 ፐርስንት ያልፋል

*** ቪክቶሪያ ውስጥ 1,313 በቫይረስ ሲጠቁ፤ አራት ሕይወታቸውን አጥተዋል።

COVID-19 update

Federal health minister Greg Hunt has said that Australia is expected to surpass 90 per cent single dose vaccination target by 1 PM today. Source: AAP

  • የፌዴራል ጤና ሚኒስትር ግሬግ ሃንት የመጀመሪያ ዙር ክትባት የተከተቡ አውስትራሊያውያን ቁጥር 90 ፐርሰንት የሚያልፍባትን የዛሬዋን ቀን 'በዕለተ ምዕራፍነት' ጠርተዋል። 
  • የፈዋሽ ቁሶች አስተዳደር የሞደርና ኮቪድ-19 ክትባት ስፓይክቫክስ SPIKEVAX ዕድሜያቸው ከ6-11 ላሉ ልጆች እንዲሰጥ ይሁንታ ቸረ።  
  • የኩዊንስላንድ ፕሪሚየር አናስታዥያ ፓለሼ ተያያዥነት የሌለው የቫይረስ ክስተት ጎልድ ኮስት ላይ ከተገኘ ተጨማሪ ገደቦች ሊጣሉ እንደሚችሉ አሳሳቡ
  • አውስትራሊያ ካፒታል ቴሪቶሪ ውስጥ ለ33 ነዋሪዎች በቫይረስ  መጠቃት ምንጩ ከአንድ ሕጋዊ ያልሆነ የሃለዊን ፓርቲ ጋር ተያይዟል
  • 80 ፐርሰንት የታዝማኒያ ነዋሪዎች ሙሉ ክትባት ተከትበዋል
  • ፊጂ ከዲሴምበር 1 ጀምሮ ድንበሮቿን ለአውስትራሊያ ከት የምታደርግ ሲሆን፤ የፊጂ ፓስፖርት ባለቤት፣ ሙሉ ክትባት የተከተቡ ባለ ይለፍ ፈቃድና ተመላሽ ነዋሪዎች ወደ ፊጂ መጓዝ ይችላሉ  

ኮቪድ-19 ስታቲስቲክስ፤

ቪክቶሪያ ውስጥ 1,313 በቫይረስ ሲጠቁ፤ አራት ሕይወታቸውን አጥተዋል።  
ኒው ሳውዝ ዌይልስ 261 ነዋሪዎቿ በቫይረስ መጠቃታቸውንና የአንድ ሰው ሕይወት ማለፉን አስታወቀች። 
ኩዊንስላንድ ውስት ሁለት ሰዎች በቫይረስ ተይዘዋል፤ አንደኛው አሁን ተከስቶ ካለው የቫይረስ ወረርሽኝ ጋር ተያያዥ አይደለም።

የወሸባና ምርመራ መመዘኛዎች የሚከናወኑትና ግብር ላይ እንዲውሉ የሚደረጉት በክፍለ አገራት መንግሥታት ነው፤

ወደ ባሕር ማዶ መጓዝ ካሹ፤ ከገደብ ነፃ የሚያደርግዎትን ይሁንታ ለማግኘት ማመልክቻዎን በኦላይን ማቅረብ ይኖርብዎታል። አውስትራሊያን ለቅቆ ለመውጣት ስለሚያስችሉ ሁኔታዎች ተጨማሪ መረጃ ለማግኘት ይህን ይጫኑ Click here. ዓለም አቀፍ በረራዎችን በተመለከተ በመንግሥት በየጊዜው የሚደረጉ ክለሳዎችና ማሻሻያዎች በ Smart Traveller ድረ ገጽ ላይ ይሰፍራሉ።





በኒው ሳውዝ ዌይልስ መድብለባሕላዊ ጤና ኮሙኒኬሽን ግልጋሎቶች የተተረጎሙ መረጃን ለማግኘት ከዚህ በታች ያሉ ሊንኮችን ይጫኑ፤

የምርመራ ክሊኒኮች በየክፍለ አገራት፤


NSW 
ACT 

የወረርሽኝ አደጋ ክፍያ መረጃ በየክፍለ አገራት፤

NSW 
ACT 

Share

Published

By SBS/ALC Content
Presented by Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service