የኒው ሳውዝ ዌይልስ 825 ነዋሪዎች በኮቪድ-19 ተጠቁ

*** ሪጂናል ቪክቶሪያ ላይ ከዛሬ ከቀትር ሰዓት በኋላ ጀምሮ የኮሮናቫይረስ ገደብ ተጣለ

COVID-19 update

Source: AAP

  • ቪክቶሪያ በዛሬው ዕለት 61 ሰዎች በቫይረስ ተይዘውባታል፤ በመላው ክፍለ አገሪቱ ላይ ገደብ ተጥሏል 
  • ኒው ሳውዝ ዌይልስ ውስጥ የኮሮናቫይረስ ወረርሽ ከተከሰተ ወዲህ ከፍተኛው በቫይረስ የተጠቁ ሰዎች ቁጥር ተመዘገበ 
  • ኩዊንስላንድ አንድም ሰው በቫይረስ ያልተያዘበትን ሁለተኛ ቀን አስቆጠረች 
  • የአውስትራሊያ ካፒታል ቴሪቶሪ ስምንት ሰዎች በቫይረስ የተጠቁባት ሲሆን አንዳቸውም የማኅበረሰብ ተጋቦት አይደሉም 

ኒው ሳውዝ ዌይልስ
ኒው ሳውዝ ዌይልስ 825 ነዋሪዎቿ በቫይረስ የተጠቁባት መሆኑን በዛሬው ዕለት አስታወቀች፤ የሶስት ሰዎች ሕይወትም አልፏል። ሟቾቹ አንድ 90ዎቹ ውስጥ የነበሩና ያልተከተቡ አረጋዊ፣ አንድ በ80ዎቹ የነበሩ ሙሉ ክትባት የተከተቡና አንዲት በ90ዎቹ ዕድሜ ያሉና አንድ ጊዜ ብቻ የተከተቡ አረጋዊት ይናቸው። 

 vaccination appointments ቫይረስ ተስፋፍቶ ባለባቸው የአካባቢ መንግሥት ሥፍራዎች ነዋሪ ሆነው ዕድሜያቸው ከ16 እስከ 39 ያሉ ግለሰቦች የኮቪድ-19 ፋይዘር ቀጠሮ አስይዘው መከተብ ይችላሉ። 

ቪክቶሪያ
ቪክቶሪያ በዛሬው ዕለት 61ነዋሪዎቿ በኮሮናቫይረስ ተጠቅተዋል። 39ኙ ወሸባ ገብተው ያሉ ናቸው።

ሪጂናል ቪክቶሪያ ውስጥ በርካታ ሰዎች በቫይረስ መያዝን ተከትሎ ከዛሬ 1pm ጀምሮ ሪጂናል ቪክቶሪያ ላይ ገደብ ተጥሏል። 

ከሰዓት ዕላፊ በስተቀር ሜልበር ላይ ተጥለው ያሉት ገደቦች በሙሉ ሪጂናል ቪክቶሪያ ላይ የፀኑ ይሆናሉ።  

የመመርመሪያ ጣቢያዎችን ማወቅ ከፈለጉ ይህን ይጫኑ list of exposure sites በአቅራቢያዎ የሚገኙ የክትባት ማዕከላትን ማወቅ ካሹ ይህን ይጫኑ list of vaccination centres.

ያለፉት 24 ሰዓታት በአውስትራሊያ ዙሪያ


Share

Published

Presented by Kassahun Seboqa Negewo
Source: SBS

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service