የአውስትራሊያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዜጎች በአስቸኳይ ኢትዮጵያን ለቅቀው እንዲወጡ አስቸኳይ ማሳሰቢያ አወጣ።
የሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ ኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙ አውስትራሊያውያን የፀጥታ ሁኔታው በፍጥነት እያሽቆለቆለ ባለበት ወቅት የአስቸኳይ ጊዜ በረራዎች ይኖራሉ ብለው እንዳይጠብቁም ምክረ ሃሳቡን ቸሯል።
ከኢትዮጵያ ለመውጣት አሁን የንግድ በረራዎች እንዳሉና የከፉ ሁኔታዎች ከተከሰቱ ግና የንግድ በረራዎች ሊታገዱ እንደሚችሉ አመላክቷል።
አዲስ አበባ የሚገነው የአውስትራሊያ ኤምባሲ ሁኔታዎችን በቅርበት እየተከታተለ ስለመሆኑና ፖሊስ አውስራሊያውያንን ጨምሮ ለእሥራት ያበቃቸው ሰዎች መኖራቸውን እንደሚያውቅም ገልጧል።
በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያን አስመልክቶ ያለው የጉዞ ማሳቢያ "አይጓዙ" (ደረጃ 4) ነው።
ከኢትዮጵያ ለቅቆ መውጣትን አክሎ አስቸኳይ የቆንስላ እርዳታ የሚሹ አውስትራሊያውያን ወደ ቆንስላው የአስቸኳይ ጊዜ ማዕከል በስልክ ቁጥር +61 2 6261 3305 መደወል ይችላሉ።
ለተጨማሪ የጉዞ ማሳሰቢያ መረጃ ይህን ይጫኑ here

