የአውስትራሊያ ኢሚግሬሽን ሚኒስትር አሌክስ ሆክ ያላቸውን የሚኒስትርነት ጣልቃ የመግባት መብት በመጠቀም የቴኒስ ኮከብ የሆነው ኖቫክ ጆኮቪችን ቪዛ ለሁለተኛ ጊዜ ሰረዙ ።
ባሳለፍነው ስኞ የፌደራል ሰርኪዩት ኮርት የተሰረዘውን የኖቫክ ጆኮቪች ቪዛ ውሳኔ ቀልብሶ ከከኢሚግሬሽን ማቆያ ስፍራ እንዲወጣ ወስኖ ነበር።
ሚስተር ሆክ እንዳሉት ቪዛው የተሰረዘው የጤናን እና የህብረተሰብ ፍላጎት መሰረት ባደረግ መልኩ ነው። አያይዘውም ውሳኔያቸውን ላማለፍም የሆም አፌርስ እና የአውስትራሊያን ቦርደር ፎርስ እንዲሁም ከጆኮቪች የተገኙትን መረጃዎች በጥልቀጥ እንዳጤኑ ተናግረዋል ።
ሰርቢያዊው የቲኒስ ተጫዋች በመጪው ሰኞ ለሚጀመረው አውስትራሊያን ኦፕን ላይ ለመወዳደር በመዘጋጀት ላይ ነበር።
Share

