በኮቪድ 19 ወረርሽኝ እና የወቅቱ የጸጥታ ሁኔታ ምክንያት የሆራ ፊንፊኔ የኢሬቻ ክብረ በዓል በውስን ሰው እንዲከበር መወሰናቸውን የኦሮሞ አባገዳዎች ህብረት ገለጸ፡፡
ህብረቱ በሆራ ፊንፊኔ የኢሬቻ ክብረ በዓል አከባበር በተመለከተ በዛሬው እለት መግለጫ ሰጥቷል፡፡
አባገዳዎቹ በመግለጫቸው እንዳሉት በዓሉ በውስን ሰው እንዲከበር ያስፈለገበት ምክንያት የኮቪድ 19 ወረርሽኝ የበለጠ እንዳይስፋፋ እና የወቅቱ የጸጥታ ሁኔታ በምክንያትነት ጠቅሰዋል፡፡
ህብረተሰቡም እራሱን እና ቤተሰቡን ከኮቪድ 19 በመጠበቅ በአባ ገዳዎች ህብረት በተቀመጠው አቅጣጫ መሠረት በዓሉን እንዲያከብር አባገዳዎቹ አሳስበዋል፡፡
የኢሬቻ በዓል የሰላም ፣ የፍቅር እና የምስጋና በዓል ነው ያሉት አባ ገዳዎቹ ፣መላው የኦሮሞ ወጣት በዓሉን ከፖለቲካ በጸዳ መንገድ እንዲያከብር ጥሪ ማስተላለፋቸውን ከአዲስ አበበ ከተማ ፕሬስ ሴክሬተሪያት ያገኘነው መረጃ ያመለክታል፡፡
- ኢቴ

