የዩናይትድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አንቶኒ ብሊንከን ከጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ ጋር በስልክ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ መነጋገራቸውን ጁላይ 6 ባወጡት መግለጫ አስታወቁ።
አቶ ብሊንከን በግጭት ላይ ባሉ ሁሉም ወገኖች ዘንድ አስቸኳይና ዘላቂ ተኩስ የማቆሙን አስፈላጊነት አንስተው ማሳሰባቸውንና የተከዜ ድልድይ መፍረስንም አስመልክቶ ማውገዛቸውን ጠቅሰዋል።
አያይዘውም፤
- የኤርትራ ጦርና የአማራ ሚሊሺያ ከትግራይ ሙሉ በሙሉ ለቅቀው እንዲወጡ
- ሰብዓዊ እርዳታን ለሚሹ ረድኤት ለመድረስ ሙሉ ተደራሽነት እንዲኖር
- በሰብዓዊ መብቶች ጥሰት ተጠያቂ በሆኑት ላይ ግልፅ የሆነ ሂደት እንዲዘረጋ
- የኢትዮጵያን የውስጥ ወሰኖችንም ሆነ ዓለም አቀፍ ድንበር በኃይል ወይም ሕገ መንግሥቱን በመጣስ መለወጥ እንደሌለበት
- ኢትዮጵያ ውስጥ ሰፍኖ ያለውን የጎሳና ፖለቲካ ክፍፍሎች ሁሉን አቀፍ በሆነ ዘላቂ መፍትሔ የሚያስገኝ ፖለቲካዊ ውይይት እንዲካሔድ በተባበሩት መንግሥታት ፀጥታ ምክር ቤት የተመከረበትን ግብር ላይ እንሲያውሉ ያበረታቱ መሆኑን ጠቅሰዋል።
የስልክ ንግግሩን አስመልክቶ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ ቢሮ እስካሁን የተሰጠ መግለጫ የለም።
Share

