የኢትዮጵያ መንግሥት አዲስ አበባ ለሚገኘው የዩናይትድ ስቴትስ ኤምባሲ ማሳሰቢያ ሰጠ

*** የኤምባሲው ድርጊት የሁለቱን አገራት ታሪካዊ ግንኙነት የሚጎዳ እንደሆነም ተመልክቷል

SBS Amharic

Source: SBS Amharic

የመንግሥት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ከበደ ዴሲሳ የአሜሪካ ኤምባሲና ድርጅቶች የሀሰት መረጃዎችን ማሰራጨት መቀጠላቸውን ጠቅሰው ከድርጊታቸውም እንዲቆጠቡ ኣሳስበዋል።

ሚኒስትር ደኤታው ‘ከዚህ ቀደም አዲስ አበባ ተከባለች’ የሚል መረጃን ያሰራጩ እንደነበር አውስተው፤ አሁን ደግሞ ‘ሽብር ይፈፀማል’ የሚል የሃሰት መረጃዎችን ያስራጫሉ ሲሉ ተናግረዋል።

አክለውም፤ ኤምባሲው ከራሱ አልፎ ሌሎች ኤምባሲዎችንና ተቋማትን እንዲወጡ ጫና እያሳደረ ነው ሲሉ ቅሬታቸውን ያሰሙ ሲሆን፤ ድርጊቱ የሁለቱን አገራት ታሪካዊ ግንኙነት የሚጎዳ መሆኑንም አመላክተዋል።

ፋና እንደዘገበው ‘የአሜሪካ እርዳታ ድርጅቶች እርዳታ ትተን እንወጣለን’ የሚል ማስፈራሪያ ማንሳታቸው ይሰማል ያሉት አቶ ከበደ፤ 'ኢትዮጵያውያን ክብራችን በስንዴ አንለውጥም' ብለዋል።


1 min read

Published

By Stringer Report


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now