የመንግሥት ኮሚኒኬሽን አገልግሎት ሚኒስትር ዴኤታ ከበደ ዴሲሳ የአሜሪካ ኤምባሲና ድርጅቶች የሀሰት መረጃዎችን ማሰራጨት መቀጠላቸውን ጠቅሰው ከድርጊታቸውም እንዲቆጠቡ ኣሳስበዋል።
ሚኒስትር ደኤታው ‘ከዚህ ቀደም አዲስ አበባ ተከባለች’ የሚል መረጃን ያሰራጩ እንደነበር አውስተው፤ አሁን ደግሞ ‘ሽብር ይፈፀማል’ የሚል የሃሰት መረጃዎችን ያስራጫሉ ሲሉ ተናግረዋል።
አክለውም፤ ኤምባሲው ከራሱ አልፎ ሌሎች ኤምባሲዎችንና ተቋማትን እንዲወጡ ጫና እያሳደረ ነው ሲሉ ቅሬታቸውን ያሰሙ ሲሆን፤ ድርጊቱ የሁለቱን አገራት ታሪካዊ ግንኙነት የሚጎዳ መሆኑንም አመላክተዋል።
ፋና እንደዘገበው ‘የአሜሪካ እርዳታ ድርጅቶች እርዳታ ትተን እንወጣለን’ የሚል ማስፈራሪያ ማንሳታቸው ይሰማል ያሉት አቶ ከበደ፤ 'ኢትዮጵያውያን ክብራችን በስንዴ አንለውጥም' ብለዋል።
Share

