የአየር መንገዱ የአውሮፕላን ጥገና ባለሙያዎች ከፍተኛ መጠን ያለው ነዳጅን እና የካርቦን ልቀትን ለመቀነስ የሚያስችል የአውሮፕላን ክንፍ ላይ የምህንድስና ማሻሻያ /winglet modification/ አደርገዋል ሲል አይዓይን ኒውስ ዘግቧል።
ማሻሻያው በቦይንግ 767 አውሮፕላኖች ላይ የተደረገ ነው ያለው አየር መንገዱ በአፍሪካ አቪየሽን ታሪክ የመጀመሪያ ሊባል የሚችል ነው ብሏል፡፡
በአመት እስከ 500 ሺህ ጋሎን ነዳጅ ለመቆጠብ እና 277 ሺህ ሜትሪክ ቶን የካርበን ልቀትን እንደሚያስቀርም ነው የገለጸው፡፡
ይህ አየር መንገዱ በአካባቢ ጥበቃ የሚያደርገውን ጥረት የሚያግዝ ነው ያለም ሲሆን የማሻሻያ ፕሮጄክቱ በ69 የአየር መንገዱ የአውሮፕላን ጥገና ባለሙያዎች ጥረት መሳካቱን አስታውቋል፡፡
Share

