በአሮጌው የኢትዮጵያ ብር መገበያየት ዛሬ ያከትማል

*** የብር ኖት ቅያሪ ታኅሳስ 6 ያበቃል

Ethiopian new currency

A cash withdrawal of Ethiopian Birr at a bank in Addis Ababa. Source: Getty Images

በአሮጌው የኢትዮጵያ ብር ኖት መገበያየት ከዛሬ ማክሰኞ ኅዳር 22 - 2013 ጀምሮ የሚያከትም መሆኑን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ አስታወቀ።

ብሔራዊ ባንኩ የአሮጌው የኢትዮጵያ ብር ኖት ቅያሬም ታህሳስ 6 - 2013 እንደሚያበቃ ገልጧል።

በዛሬው ዕለት የሚያበቃው የአሮጌ ብር ኖት ግብይት ለብር ኖት ቅያሪው መፋጠን የበኩሉን አስተዋፅዖ እንደሚያበረክትና ለብር ቅያሬው የቀሩት ቀናት 15 ቀናት ብቻ መሆናቸውን ባንኩ አስገንዝቧል።

በቀሪዎቹ ሁለት ሳምንታት አሮጌዎቹ የብር ኖቶች በእጃቸው የሚገኙ ሰዎች ከታህሳስ 6 በፊት ወደ ባንክ ሄደው ሕጋዊ ቅያሪ እንዲያደርጉ ብሔራዊ ባንኩ በድጋሚ ጥሪ አድርጓል። 

አሮጌ የብር ኖቶችን በአዲስ የብር ኖቶች መቀየር የተጀመረው ከመስከረም 6 - 2013 ጀምሮ ነው።

 


1 min read

Published

By Stringer Report


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now