Watch FIFA World Cup 2026™

LIVE, FREE and EXCLUSIVE starting June 12 2026

አቡነ ማትያስ በአርሲ ሀገረ ስብከት በቤተ ክርስቲያናትና በምእመናን ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶች እንዲቆሙ ጥሪ አቀረቡ

ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ በአርሲ ሀገረ ስብከት በቤተ ክርስቲያናትና በምዕመናን ላይ እየደረሱ ነው ያሏቸው ጥቃቶች እንዲቆሙ ለፀጥታ አካላት ጥሪ አቀረቡ። ፓትርያርኩ ጥሪያቸውን ያቀረቡት በአርሲ ሀገረ ስብከት በተለያዩ አካባቢዎች በቤተ ክርስቲያን ንብረቶችና በምዕመናን ላይ የደረሱ ጉዳቶችን በማስመልከት ባስተላለፉት መልዕክት ነው።

gettyimages-1247013345-612x612.jpg
Abune Mathias, Patriarch of the Ethiopian Orthodox Tewahedo Church, prays during a press conference in Addis Ababa, Ethiopia, on 11 February 2023. Credit: AMANUEL SILESHI/AFP via Getty Images

ብፁዕነታቸው በመልዕክታቸው እንደገለጹት፣ በተለይም በአሰኮ፣ በሽርካ፣ በሆንቆሎ፣ በዋቤና በሙኔሳ ወረዳዎች በቤተ ክርስቲያናትና በምእመናን ላይ የተፈጸሙ ጥቃቶች ከፍተኛ ጉዳት ማስከተላቸውን ገልጸዋል።

የብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ ልዩ ጽሕፈት ቤት ባወጣው መግለጫ መሠረት፣ በእነዚህ ጥቃቶች ምክንያት ከአንድ ምዕተ ዓመት በላይ ያስቆጠረው የጠላታ ቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን በእሳት መቃጠሉ ተገልጿል።

በተጨማሪም የካራ ኩፍቴና መድኃኔ ዓለም ቤተ ክርስቲያን መዘረፉንና የቤተ ክርስቲያኑ ንብረቶች ለጉዳት መዳረጋቸውን መግለጫው አመልክቷል።

መግለጫው አክሎም በርካታ ምእመናን በግፍ መገደላቸውን እና በመቶዎች የሚቆጠሩ ዜጎች ከመኖሪያ ቀዬያቸው መፈናቀላቸውን ገልጿል። በአካባቢው የተፈጠረው ሁኔታ በማኅበረሰቡ ዘንድ ከፍተኛ ስጋት እና የደኅንነት ችግር መፍጠሩም ተጠቁሟል።

 አቡነ ማትያስ በመልዕክታቸው የዜጎችን ደኅንነት የመጠበቅና ሰላምን የማስፈን ሕጋዊ እና ሞራላዊ ኃላፊነት የተጣለባቸው የጸጥታ አካላት በቤተ ክርስቲያናትና በምእመናን ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን በአስቸኳይ እንዲያስቆሙ አሳስበዋል። እንዲሁም በጥቃቶቹ ውስጥ ተሳትፈዋል የተባሉ ግለሰቦችና ቡድኖች ተገቢውን የሕግ ተጠያቂነት እንዲወስዱ ጠይቀዋል።

በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች የሚገኙ ምዕመናንና መላው ኢትዮጵያውያን በጥቃቶቹ ሳቢያ ከቀዬአቸው የተፈናቀሉ ወገኖችን በሰብአዊ ድጋፍ፣ በአጋርነት እና በማጽናናት እንዲያግዙ፣ የሀገሪቱ ሰላምና አንድነት እንዲጠናከር፣ ዜጎችም ከጥቃትና ከመፈናቀል እንዲጠበቁ ሁሉም አካላት የበኩላቸውን ኃላፊነት እንዲወጡ ጥሪ አቅርበዋል።

 


1 min read

Published

By Demeke Kebede

Source: SBS


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Stream now