ፌስቡክ አውስትራሊያ ላይ ጥሎ የነበረውን የዜና ስርጭቶች ዕገዳ ነገ ሊያነሳ ነው

*** ፌስቡክ የተወሰኑ ለውጦችን ያደርጋል ተብሎ ይጠበቃል

SBS Amharic

Source: SBS Amharic

ነገ ዓርብ ፌብሪዋሪ 26 ፌስቡክ የአውስትራሊያ የዜና ገጾች ላይ ጥሎ የነበረውን ዕገዳ እንደሚያነሳ በጅሮንድ ጆሽ ፍራይደንበርግ አስታወቁ።

አክለውም "ከነገ ጀምሮ የተወሰኑ ለውጦችንም ታያላችሁ፤ ፌስቡክ እንዲያ ብሎ ነግሮናል" ሲሉ ለሬዲዮ 2GB ዛሬ ማምሻው ላይ ተናገረዋል።

ፌስቡክ ካለፈው ሳምንት ጀምሮ አውስትራሊያ ውስጥ ያሉ አታሚዎችና ተጠቃሚዎች የአገር ውስጥና የባሕር ማዶን ዜናዎችና ታሪኮች ማጋራትና መመልከት እንዳይችሉ ዕገዳ ጥሎ አለ።

ለዕገዳው መጣል አስባብ የሆነው የአውስትራሊያ ፌዴራል መንግሥት ከጥቂት ቀናት በፊት በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤትና በዛሬው ዕለት ይሁንታ ያገኘው የሚዲያ ረቂቅ ድንጋጌ ነበር።

ረቂቅ ድንጋጌው ፌስቡክ ገጾቹ ላይ ለሚያሰፍራቸው የአውስትራሊያ ዜናዎች ክፍያ እንዲፈጽም ግድ የሚል ነው።

ሆኖም ዕገዳ ከጣለ በኋላ በፌዴራል መንግሥቱና ፌስቡክ መካከል በተደረጉ ድርድሮች ረቂቅ ድንጋጌው ላይ ማሻሻያዎች በመደረጋቸው ከአግባቢ ስምምነት ላይ መድረስ ችለዋል።     

 


1 min read

Published

By NACA

Presented by Kassahun Seboqa Negewo


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now