የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ጃኑዋሪ 20 በሚካሔደው የጆ ባይደን ፕሬዚደንታዊ ቃለ መሃላ ሥነ ሥርዓት ላይ እንደማይገኙ አስታወቁ።
17ኛው የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት አንድሩ ጆንሰን በ1869 በተኪያቸው 18ኛው የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚደንት ዩልየሲስ ግራንት ፕሬዚደንታዊ ቃለ መሃላ ላይ አልገኝም ካሉ 152 ዓመታት በኋላ ፕሬዚደንት ትራምፕ ሁለተኛው ፕሬዚደንት ሆነዋል።
ዶናልድ ትራምፕ ይህንኑ በዓርቡ የቲዊተር መልዕክታቸው ገልጠዋል።

ተመራጭ-ፕሬዚደንት ጆ ባይደን በበኩላቸው የትራምፕን በቃለ መሃላ ሥነ ሥርዓት ላይ አልገኝም ማለትን "ጥሩ ነገር" ነው ብለውታል።
አቶ ባይደን "ወደ እዚህ እየመጣሁ ሳለ በቃለ መሃላ ሥነ ሥር ዓቱ ላይ የማይገኙ መሆኑን ወደ እዚህ እየመጣሁ ነው። እኔና እሳቸው ከምንስማማባቸው ጥቂት ነገሮች አንዱ ይህ ነው። የእሳቸው አለመገኘት ጥሩ ነገር ነው። ለአገሪቱ ማፈሪያ ናቸው" ሲሉ ከነበሩበት ዊልሚንግተን - ዴላዌር ተናግረዋል።

ባይደን የምክትል ፕሬዚደንት ማይክ ፔንስ በሥነ ሥርዓቱ ላይ መገኘትን በመልካም ጎኑ እንደሚቀበሉት ገልጠዋል።

