በጥይት የቆሰሉት የቀድሞው የጃፓን ጠቅላይ ሚኒስትር ሕይወታቸው ሳያልፍ እንዳልቀረ ሪፖርቶች እየጠቆሙ ነው

*** የ67 ዓመቱ የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር ሺንዞ አቤ ወደ ሆስፒታል ሲወሰዱ ከአንገታቸው ደም እየፈሰሰ እንደነበር የጃፓኑ የዜና አውታር ጂጂ ዘግቧል።

Former Prime Minister Shinzo Abe

Former Prime Minister Shinzo Abe makes a street speech before being shot in front of Yamatosaidaiji Station on July 8, 2022 in Nara, Japan. Source: Getty

የቀድሞው መሪ በጥይት የተመቱት ዛሬ ዓርብ ጁላይ 8 / ሐምሌ 1 እሑድ ለሚካሔደው ለሊብራል ዲሞክራት ፓርቲ የሕግ መወሰኛ ምክር ቤት ምርጫ የቅስቀሳ ንግግር እያደረጉ ሳለ ነው። 

ሁኔታውን አስመልክተው የጃፓን ባለስልጣናት እንደገለጡት አቤ በአየር ትራንስፖርት ወደ ሆስፒታል ሲወሰዱ ትንፋሽ እንዳልነበራቸውና የልብ ትርታቸው ቆሞ እንደነበር ጠቅሰዋል።

የህዝብ ብዙኅን መገኛው NHK የቀድሞው ጠቅላይ ሚኒስትር በጥይት ተመትተው እንደወደቁ የሚያሳያውን ምስል ለእይታ አቅርቧል።
News
Former Prime Minister Shinzo Abe bleeds from chest after being shot in front of Yamatosaidaiji Station on July 8, 2022 in Nara, Japan. Source: Getty
የአቤ በጥይት መመታት ለሕዝብ ይፋ የሆነው ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ነው። 

የአደጋውን ዜና የሰሙትና በምርጫ ቅስቀሳ ዘመቻ ላይ የነበሩት የቀቅቱ ጠቅላይ ሚኒስትር ፉሚዮ ኪሺዳ የምርጫ ቅስቀሳቸውን አቋርጠው በሂሊኮፕተር ወደ ቶኪዮ አቅንተዋል፤ ሁሉም የካቢኔ አባላት የምርጫ ቅስቀሳቸውን አቋርጠው ቶኪዮ እንዲገቡ ትዕዛዝ አስተላልፈዋል። 

አቤ በ2020 በጤና ምክኛት ከተቅላይ ሚኒስትርነት ኃላፊነታቸው መልቀቃቸው ይታወሳል። 

አቤ በተለይም ጃፓንን ከጦርነት የሚያርቀውን ሕገ መንግሥት ለመለወጥና የአገሪቱን የመከላከያ ኃይል ኮሪያና ቻይናን በብርቱ በሚቀናቀን መልኩ ለመቅረፅ እንዲያስችል በፓርላማ ማሳለፋቸው በሕዝብ ዘንድ ፅኑዕ ቁጣን፣ በተወሰኑት ዘንድም የከፋ አተያይን አስነስቶባቸው ነበር።

የአቤ ደጋፊዎች በበኩላቸው የጃፓንና ዩናይትድ ስቴት ስን ኝኙነት ጠንካራ ደረጃ እንዲደርስ ማድረጋቸው አንዱ የመታሰቢያ አሻራቸውን እንደሆን ተናግረዋል። 

የአውስትራሊያ ጠቅላይ ሚኒስትር አንቶኒ አልባኒዚ፣ የዩናይትድ ስቴት ስ ባለስልጣናትና የቀድሞው ፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ በክስተቱ መደናገጣቸውንና ከልብ ማዘናቸውን ገልጠዋል። 

 


Share

Published

By Stringer Report

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service