የጋምቤላ ክልል ምክር ቤት አቶ ኡሞድ ኡጁሉን የክልሉ ርዕሠ-መስተዳድር አድርጎ መርጧል፡፡
አቶ ኡሞድ ኡጁሉ የክልሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት፣ የክልሉ ስነ ምግባርና ጸረ ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽነር እንዲሁም ከህዳር 1/2011 ዓ.ም ጀምሮ የክልሉ ርእሠ መስተዳድር ሆነው ያገለገሉ ሲሆን ለቀጣይ አምስት ዓመታት የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ሆነው እንዲያገለግሉ ተመርጠዋል።
[ ጋምቤላ ኮሙኒኬሽን ]
***
የሲዳማ ክልል ምክር ቤት ባካሔደው የስድስተኛው ዙር የመጀመሪያ ጉባኤው አቶ ደስታ ዳሌሞን በርዕሰ መስተዳድርነት መርጣል።
ለቀጣዩ አምስት በጉባእኤው የተመረጡት አቶ ደስታም በርዕሰ መስተዳድርነት ቃለ መሃላ ፈጽመዋል።
Share

