የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር ዛሬ ይጀመራል

*** የግብፅ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር በስበሰባው ላይ ላይሳተፉ ይችላሉ

GERD talks

Source: PD

የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቃል አቀባይ አምባሳደር ዲና ሙፍቲ የታላቁ የኢትዮጵያ ሕዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር ዛሬ ማክሰኞ ከቀትር በኋላ መካሄድ እንደሚጀምር ገልጠዋል።

ምንም እንኳ ቃል አቀባዩ በድርድሩ ላይ የኢትዮጵያ፣ ሱዳንና ግብጽ የውሃ ጉዳይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሮች እንደሚሳተፉ ቢገልጡም በግብፅ የዜና አውታሮች የግብፅ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ሳሜህ ሹክሪ ቀደም ብሎ በተያዘ የውጭ አገር ጉዞ ፕሮግራም ሳቢያ ምናልባትም በስብሰባው ላይ ላይታደሙ እንደሚችሉ ጠቁመዋል።

የግብፅ የውኃና የመስኖ ሚኒስትር መሐመድ ኤል-ሳባይ በበኩላቸው ግብፅ በስብሰባው ላይ ሙሉ ተሳትፎ እንደምታደርግና ልዩነቶችን ፈጥረው ባሉት ሕጋዊና ቴክኒካዊ ጉዳዮች ላይ እንደምታተኩር ገልጠዋል። 

የሱዳን የመስኖ ሚኒስትር ያሲር አባስ ሱዳን ሙሉ ተሳትፎ እንደምታደርግና ድርድሩን ከእልባት ላይ ለማድረስ የሚያግዝ አዲስ የመደራደሪያ ማዕቀፍ ይዘው እንደሚቀቡ ተናግረዋል። 

በአፍሪካ ህብረት አደራዳሪነት ሲካሄድ የቆየው የሕዳሴ ግድብ የሶስትዮሽ ድርድር ለሰባት ሳምንታት ሲካሄድ ቆይቶ በግብፅ የውኃ ሙሌትና አስገዳጅ ድንጋጌ እከላ ጥየቃ ነሐሴ 22 ቀን 2012 ዓ.ም ከተካሄደው የበይነ መረብ ውይይት በኋላ መቋረጡ የሚታወስ ነው።

አምባሳደር ዲናም በፊናቸው ኢትዮጵያ በሶስትዮሽ ድርድሩ የኢትዮጵያን ብሔራዊ ጥቅምና መብት ባስከበረ መልኩ ድርድሩን እንደምታካሂድ ገልጠዋል።

የሶስትዮሽ ድርድሩ ስኬታማ እንዲሆን ኢትዮጵያ ፅኑ ፍላጎት እንዳላትም ቃል አቀባዩ ተናግረዋል።

 

 

 

 

 


1 min read

Published

Updated

By Stringer


Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps

Watch on SBS

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service

Watch now