ወታደራዊ ጠቀሜታዋ የጎላ እንደሆነ የሚነገርላትን ጋሸና ከተማን እንደተቆጣጠረ የኢትዮጵያ መንግስት አስታወቀ

*** በወረኢሉ ግንባር የጃማደጎሎ ወረኢሉ ገነቴ፣ ፊንጮፍቱ፣ አቀስታ ከተሞች ፤ እንዲሁም በሸዋ ግንባር የመዘዞ፣ ሞላሌ፣ ሸዋሮቢትና አካባቢው፣ ራሳና አካባቢው ከሕወሓት እጀ መውጣታቸው በመንግሥት ኮሙኒኬሽን አገልግሎት በኩል ተገልጧል

Homeland Report

Source: EPA

የመንሥት ኮሙንኬሽን አገልግሎት ሚኒስትሩ ዶ/ር ለገሰ ቱሉ ዛሬ ለመንግድድት መገናኛ ብዙኃን በሰጡት የቀጥታ ስርጭት መግለጫ እንዳሉት “በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አህመድ እየተመራ በሁሉም ግንባሮች ወደ ከፍተኛ የማጥቃት እንቅስቃሴ የገባው የ"ዘመቻ ለኅብረ ብሔራዊ አንድነት" ከፍተና ውጤቶችን ማስመዘገቡን ገለጡ፡፡

ዶር ለገሰ ስትራቴጂካዊ ጠቀሜታ ባለው በጋሸና ግንባር የአገር መከላከያ ሠራዊት፣ የአማራ ልዩ ሀይል ሚሊሻና ፋኖ በጥምረት ባደረጉት ተጋድሎ የአርቢትን፣ የአቀትን፣ የዳቦና የጋሸና ከተሞችን ነጻ ማውጣቱን ተናግረዋል፡፡

እንደ ዶር ለገሰ ገለፃ “በዚህ ግምባር ሕወሓት ለበርካታ ወራት በወረራ የያዘውን አካባቢ ህዝብ በማስገደድ ያሰራውን ባለብዙ እርከን ኮንክሪት ምሽግ በተቀናጀ እቅድ፣ አመራርና ቴክኖሎጂ በመታገዝ በአነስተኛ መስዋዕትነት ምሽጉ ተሰብሯል። በዚህ ግንባር በርካታ የነፍስ ወከፍና የቡድን ከባድ መሳሪያዎች በወገን ጦር ተማርከዋል።” ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ መንግስት ጦር ጋሸናን መቆጣጠሩ ሕወሓት በላሊበላ፣ ወልዲያና ደሴ የተቆጣጠራቸውን አካባቢዎች በአጭር ጊዜ ውስጥ ለመቆጣጠር መንገዱን ምቹ ያደርጋል ሲሉም አክለዋል።

በሌላ መልኩ በወረኢሉ ግንባር የጃማደጎሎ ወረኢሉ ገነቴ፣ ፊንጮፍቱ፣ አቀስታ ከተሞች ነጻ ወጥተዋል ያሉት ዶር ለገሰ በሸዋ ግንባር ደግሞ የመዘዞ፣ ሞላሌ፣ ሸዋሮቢትና አካባቢው እንዲሁም ራሳና አካባቢው ነፃ ወጥተው ወደፊት እየገሰገሱ እንደሚገኙም ተናግረዋል።

በምስራቅ ግንባርም የአገር መከላከያ ሠራዊት፣ የአፋር ልዩ ሀይልና ሚሊሻ ባደረጉት ተጋድሎ ነጻ የወጡት የካሳጊታ፣ ቡርቃ ዋኢማ ጪፍቱ ድሬሩቃ፣ ጭፍራ አለሌ ሱሉላ ከተሞች ሙሉ በሙሉ ወደ አካባቢው አስተዳደር ተመልሷል ብለዋል፡፡

ከደቂዎች በፊት በሶሻል ሚዲያ ገፆቸው መልዕክት ያሰፈሩትና በግንባር የሚገኙት ጠቅላይ ኢታማዦር ሹሙ ዐቢይ አህመድ "የኢትዮጵያ ሕዝብ በሁሉም መስክ ተባብሮ ሲነሣ ውጤቱ ድል ነው። በግንባር፣ በዲፕሎማሲ፣ በኢኮኖሚ፣ በኮሙኒኬሽን፣ በስንቅ ዝግጅት፣ ዘማች በመከባከብ፣ ጸጥታ በማስከበር፣ተፈናቃዮችን በመደገፍ. በሁሉም ግንባሮች ለዘመታችሁ ሁሉ እንኳን ደስ አላችሁ" ብለዋል፡፡

በመንግሥት በኩል የተሰጠውን ወታደራዊ መግለጫ አስመልክቶ ለጊዜው በሕወሓት በኩል የተሰጠ ምላሽ አልቀረበም።

(ደመቀ ከበደ - አዲስ አበባ)


Share

Published

By Demeke Kebede

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service