የመንግሥት ኩሙኒኬሽን አገልግሎት ባወጣው መግለጫ በሶስት ወታደራዊ ግጭቶች በተካሄዱባቸው ግንባሮች ተጨማሪ ከተሞች በመንግሥት ቁጥጥር ስር መዋላቸውን አስታወቀ።
በዚህም መሠረት፤
- በጋሸና ግንባር ቀውዝባና ጭላ ከተሞችና አካባቢያቸው
- በወረኢሉ ግንባር አጅባር፣ ተንታ እና ዶባ ከተሞችና አካባቢያቸው
- በከሚሴ ግንባር ማጀቴን፣ ጭረቲን፣ ከሚሴን፣ ርቄን፣ ወለዲን፣ አልቡኮ ከተሞችን እና የቃሉ ወረዳን አብዛኛው ክፍል በመንግሥት ቁጥጥር ስር መሆናቸውን ገልጧል።
በሕወሓት በኩል ይህንን አስመልክቶ ለጊዜው ወታደራዊ መግለጫ አልተሰጠም።
Share

