የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን በቄሌም ወለጋ ዞን ዘር ተኮር ጥቃትን ለመግታት አስቸኳይ የመንግሥት ፀጥታ ኃይል ስምሪትን ጠየቀ

*** ኮሚሽኑ ተጨማሪ የሰላማዊ ሰዎች ሕይወት እንዳይቀጠፍ የመንግሥት ፀጥታ ኃይላት አፋጣኝ እርምጃዎችን እንዲወስድ አፅንዖት ሰጥቶ የዳግም ጥሪ አቅርቧል።

News

Daniel Bekele, Chief Commissioner of the Ethiopian Human Rights Commission (EHRC). Source: Getty

የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ኮሚሽን (ኢሰመኮ) ከኦሮሚያ ቄሌም ወለጋ ዞን የደረሱት የጭፍጨፋ ሪፖርቶች በእጅጉ ያሳሰቡት መሆኑን ጁላይ 4 / ሰኔ 27 ባወጣው አስቸኳይ መግለጫ አስታወቀ።

አያይዞም፤ ለጊዜው ሰለባ የሆኑ ሰዎች ቁጥርን አስመልክቶ ሙሉ የማረጋገጫ ድምዳሜውን ይፋ ባያደርግም በኦሮሚያ ሐዋ ገላን ወረዳ ቄሌም ወረዳ ዞን መንደር 20 እና መንደር 21 ውስጥ የደረሰው ዘር ተኮር ጭፍጨፋ ግና በብርቱ አሳሳቢ መሆኑን ገልጧል።

ኮሚሽኑ ሁኔታዎችን መከታተሉን እንደቀጠለ መሆኑንና ከጭፍጨፋው ከተረፉት ሰዎችና ከአካባቢው የመረጃ ምንጮቹ ጋር እየተነጋገረ ያለ መሆኑን አመላክቷል።

በመረጃ ምንጮቹ መሠረትም ጥቃት ፈፃሚዎቹ የኦሮሞ ነፃነት ሠራዊት ወይም ኦነግ ሸኔ በመባል የሚታወቀው ታጣቂ ቡድን እንደሆነና ግድያዎቹ የተካሔዱትም ሰኔ 27 ከቀትር በፊት እንደሆነ የደረሱት ሪፖርቶች ማመልከታቸውን ገልጧል። 

ኢሰመኮ የመንደር 20 እና 21 ነዋሪዎች የአማራ ዝርያ ያላቸው መሆኑን እንደተገነዘበና የመንግሥት ፀጥታ ኃይላትም በሥፍራው መድረሳቸውን አመልክቷል።

ሆኖም ነዋሪዎች ወደ ሌላ ቀዬ መጠጊያ ፍለጋ ላይ እንደሆኑም ጠቁሟል። 

የኮሚሽኑ ዋና ኃላፊ ዶ/ር ዳንኤል በቀለ ድርጊቱን አስመልክተው “በአካባቢው ሰፍኖ ያለው የደኅንነት ስጋትና ዘር ተኮርነትን የተላበሰው የነዋሪዎች ግድያ በአስቸኳይ ሊገታ ይገባል" ብለዋል።

የኮሚሽኑን ጥሪ ዳግም በማስተጋባትም ሌላ የሰላማዊ ሰዎች ሕይወት እንዳይቀጠፍ የመንግሥት ፀጥታ ኃይላት አፋጣኝ እርምጃዎችን እንዲወስድ አፅንዖት ሰጥተው አሳስበዋል።


Share

Published

By Stringer Report

Share this with family and friends


Follow SBS Amharic

Download our apps
SBS Audio
SBS On Demand

Listen to our podcasts
Independent news and stories connecting you to life in Australia and Amharic-speaking Australians.
Ease into the English language and Australian culture. We make learning English convenient, fun and practical.
Get the latest with our exclusive in-language podcasts on your favourite podcast apps.

Watch on SBS
SBS World News

SBS World News

Take a global view with Australia's most comprehensive world news service